Amhara Culture & Tourism Bureau

Amhara Culture & Tourism Bureau Government organization

"በአካባቢው አንጻራዊ ሰላም መፈጠሩ ለቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን ፈጥሮላቸዋል" የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ  ፀጋየ *****በላሊበላ የዘንድሮውን የልደት በዓል  በድምቀት ለማ...
03/01/2025

"በአካባቢው አንጻራዊ ሰላም መፈጠሩ ለቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን ፈጥሮላቸዋል" የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋየ
*****
በላሊበላ የዘንድሮውን የልደት በዓል በድምቀት ለማክበር ከክልል እስከ ከተማ አስተዳደሩ ድረስ ሰፊ ዝግጅት ተደርጓል።

በዓሉን እንደወትሮው ሁሉ በደመቀ ሁኔታ ለማክበር የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከሰሜን ወሎ ዞን እና ከላሊበላ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማከናወኑን የቢሮው ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋየ ገልፀዋል።

አቶ መልካሙ ለአሚኮ እንደገለጹት ቀደም ሲል ለሆቴሎች ክትትልና ድጋፍ ሲደረግላቸው ቆይቷል፤ ለአስጎብኝዎችና ለሆቴል ሰራተኞችም ሙያዊ ስልጠናዎች ተሰጥተዋል ብለዋል።

በተጨማሪም ከሀይማኖት አባቶች፣ ከጸጥታ አካላት፣ ከአስጎብኝ ድርጅቶች እና ከማህበረሰቡ ጋር ሰፊ ውይይቶች የተደረጉ መሆናቸውንም አብራርተዋል።

ሆቴሎችና አስጎብኝ ድርጅቶች ለቱሪስቶች ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችላቸውን ዝግጅት መጨረሳቸውንም ገልፀዋል።

አሁን ላይ ቱሪስቶች ወደ ላሊበላ መግባት መጀመራቸውን የተናገሩት አቶ መልካሙ በላሊበላ እና አካባቢዋ አንጻራዊ ሰላም መኖሩ ለቱሪስቶች ምቹ ሁኔታ ፈጥሮላቸዋል ብለዋል።

ቱሪስት ለጉዞ የሚዘጋጀውና የሚያቅደው በመዳረሻው ያለውን የሰላም ሁኔታ መሠረት በማድረግ መሆኑን ጠቅሰው ሰላምን ማስፈን ለቱሪስት እንቅስቃሴ ዋናው ቅድመ ሁኔታ መሆኑን አመልክተዋል።

አሁን ላይ ወደ ላሊበላ ከአገር ውስጥም ከአገር ውጭም ከፍተኛ ቀጥር ያላቸው ቱሪስቶች እየገቡ መሆናቸውንም አቶ መልካሙ አስታውቀዋል።

ኑ! ገናን በላሊበላ አብረን እናክብር
#ቤዛኩሉ #ገና #ላሊበላ

እልፍ ዘመናትን የተሻገረ የእንግዳ እግር አጠባ የባህል እሴት-- በላሊበላ******የልደት በዓል በላሊበላ በየዓመቱ ከአራቱም ማዕዘናት የመጡ ኢትዮጵያውያንን ያሰባስባል። ተነፋፍቀው የኖሩትን ...
03/01/2025

እልፍ ዘመናትን የተሻገረ የእንግዳ እግር አጠባ የባህል እሴት-- በላሊበላ
******
የልደት በዓል በላሊበላ በየዓመቱ ከአራቱም ማዕዘናት የመጡ ኢትዮጵያውያንን ያሰባስባል። ተነፋፍቀው የኖሩትን ባለእንጀሮች በቀጠሮ ያገናኛል። ከባህር ማዶሞ ኢትዮጵያን ለማየት የኢትዮጵያን ሰማይ አቋርጠው ላሊበላ ላይ ይከሰታሉ።

በላሊበላ ቁሳዊ ቅርስ ብቻ አይደለም ያለው። ዘመናትን የተሻገረ ድንቅ የባህል እሴት፣ ጥልቅ ማህበረሰባዊና መንፈሳዊ ሀብት ጭምር አለ።

በተለይም ለበዓል እንግዶች ወደ ላሊበላ ሲመጡ እግር በማጠብ የመቀበልና የማስተናገድ፤ ፍፁም ትህትና እና ጨዋነት በተግባር የሚገለጥበት ድንቅ ትውፊት ነው። የእንግዶችን እግር ማጠብና መቀበል ያልነጠፈ፣ እልፍ ዘመናትን የተሻገረ የላሊበላ ድንቅ እሴት ነው።

ራስን ዝቅ በማድረግ ካህናት፣ ወጣቶች፣እናቶች፣ አባቶች የእንግዶችን እግር እያጠቡ በትህትና ያስተናግዳሉ። ይህ የእንግዳ አቀባበል ስርዓት በተለይም ለውጭ ጎብኝዎች ልዩ ትኩረት የሚስብ ድንቅ ክስተት ነው።

የላሊበላ ነዋሪዎች "የእንግዶችን እግር ማጠብ መባረክ ነው" ይላሉ። "እንግዶች እንኳ በደህና መጣችሁ" እያሉ አባቶች ይመርቃሉ። ወጣቶችም እንግዶችን በንስር አይን እየተከታተሉ ደህንነታቸውን ይጠብቃሉ። ሁሌም ወደ ላሊበላ የሚሄድ ሁሉ ቤተኛ እንጅ እንግዳ አይሆንም።

ዘንድሮም እንግዶች በዓሉን ለመታደም ከውጭም ከአገር ውስጥም ወደ ላሊበላ እየገቡ ነው። ላሊበላም እንደተለመደው እንግዶቿን እግራቸውን እያጠበች በስስት እየተቀበለች ነው። ለልደት በዓል በላሊበላ ሁሉም አለ።

ገናን በላሊበላ ያክብሩ!!
#ቤዛኩሉ #ገና #ላሊበላ

"ኑ  አብረን እናክብር በዓለ መርቆሪስ በእስቴ መካነ ኢየሱስ"ወከጉና ሰማይ ስር።እስቴ መካነ እየሱስ።ከፋርጣ አጅባር እስከ እስቴ አምቦ ሜዳ።"የኔ ሀገር ወዲህ ነው፤ የአንቺስ ሀገር እስቴ  ...
03/01/2025

"ኑ አብረን እናክብር በዓለ መርቆሪስ በእስቴ መካነ ኢየሱስ"

ወከጉና ሰማይ ስር።
እስቴ መካነ እየሱስ።
ከፋርጣ አጅባር እስከ እስቴ አምቦ ሜዳ።
"የኔ ሀገር ወዲህ ነው፤ የአንቺስ ሀገር እስቴ
ብሉልኝ ጠጡልኝ የሚለው፣
"በሞቴ" ስጋና ደም ለብሶ ያየሁት እስቴ ነው።

ከፋርጣ አጅባር ሜዳ እስከ እስቴ አምቦ ሜዳ የመርቆሬዎስ ንግስ ድባብ ልዩ ነው።

#ሀገሬ #አጅባር #እስቴ
#መርቆሬዎስ #ፈረስ #ጉግስ #ጎንደር
South Gondar Zone Communication

"ኑ ተዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው" የላሊበላ ሆቴሎች ማኅበር ******የልደት በዓል በላሊበላ በድምቀት ይከበራል። ልደትን በላሊበላ ለማክበር አስቀድመው የተነሱ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገ...
03/01/2025

"ኑ ተዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው" የላሊበላ ሆቴሎች ማኅበር
******
የልደት በዓል በላሊበላ በድምቀት ይከበራል። ልደትን በላሊበላ ለማክበር አስቀድመው የተነሱ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ጎብኝዎች ላሊበላ እየገቡ ነው።

በላሊበላ ከተማ አሥተዳደር የሚገኙ ሆቴሎችም ተዘጋጅተው እንግዶቻቸውን እየተቀበሉ ነው። ገና የሚመጡትንም በጉጉት እየጠበቁ ናቸው።

የቅዱስ ላሊበላ ሆቴሎች ማኅበር ፕሬዝዳንት እና የምዘና ሪዞርት ባለቤት ዮሐንስ አሰፋ በማኅበሩ ውስጥ ከ52 በላይ ሆቴሎች እንደሚገኙ ተናግረዋል። ሆቴሎቹ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽ ጀምሮ ተቸግረው መቆየታቸውን አስታውሰዋል።

በችግር ውስጥ የቆዩት ሆቴሎች ለልደት በዓል ተዘጋጅተው እንግዶችን እየጠበቁ መኾናቸውን ነው የተናገሩት። በዓሉ እየቀረበ ሲመጣ በርካታ ጎብኝዎች እንደሚመጡ ይጠበቃል ነው ያሉት። የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንግዶች በብዛት እንዲገቡ አስቀድሞ በርካታ በረራዎችን እንዲፈቅድም ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስቀድሞ በርካታ በረራዎችን ከፈቀደ እንግዶች በስፋት ይመጣሉ። የላሊበላ የቱሪዝም እንቅስቃሴም ይነቃቃል ብለዋል።

ሆቴሎች በራቸውን ከፍተው እንግዶችን በብዛት እየጠበቁ መኾናቸውንም ገልጸዋል። የውጭ ሀገር ጎብኝዎች በዓሉ ሲቀርብ በብዛት እንደሚመጡ ይጠበቃሉ ነው ያሉት። እንግዶቻችን ኑ ተዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው ብለዋል።

ላሊበላ እና አካባቢው ብቸኛ የገቢ ምንጩ ቱሪዝም ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ ቱሪዝም ከሌለ ላሊበላ የለችም፣ ቱሪዝም እንዲነቃቃ እንፈልጋለን፣ የልደት በዓልም የቱሪዝም እንቅስቃሴውን እንደሚያነቃቃው ተስፋ አለን ነው ያሉት። ጎብኝዎች ሲመጡ የላሊበላ ሆቴሎች ብቻ ሳይኾኑ የላሊበላ ከተማ ነዋሪዎችም ተጠቃሚ እንደሚኾኑ ነው የተናገሩት።

ለቱሪዝም እንቅስቃሴ ሰላም ወሳኝ መኾኑንም ገልጸዋል። ሰላም ካለ ላሊበላ በቱሪዝም ተጠቃሚ እንደሚኾን ጥርጥር የለውም ነው ያሉት።

ሆቴሎቻችን አዘጋጀተን፣ መንገድ ጠርገን፣ ትልቅ ተስፋ ይዘን እንግዶቻችን እየጠበቅን ነው ብለዋል። የከተማ ነዋሪዎች የተሻለ እንግዶችን እግር እያጠቡ፣ ካላቸው ላይ ለእነርሱ እየሰጡ መኾናቸውን ገልጸዋል።

እንግዶች ቢመጡ ላሊበላን በሰላም ጎብኝተው እንደሚመለሱ ማረጋገጥ እንችላለን። ከመምጣታቸውም አስቀድሞ ማረጋገጥ ይችላሉ ነው ያሉት። ልደትን አብረውን እንዲያከብሩም ጥሪ ማቅረባቸውን አሚኮ ዘግቧል።

ለልደት በዓል አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የሰሜን ወሎ ዞን ባሕል እና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ። ***የሰሜን ወሎ ዞን ድንቅ የኾኑ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን፣ አሸንድየ እ...
03/01/2025

ለልደት በዓል አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን የሰሜን ወሎ ዞን ባሕል እና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።
***
የሰሜን ወሎ ዞን ድንቅ የኾኑ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን፣ አሸንድየ እና ሶለልን የመሰሉ ድንቅ ባሕላትን እና ሌሎች አያሌ የቱሪዝም ሃብቶችን የያዘ አካባቢ ነው።

ዞኑ በቅዱስ ላሊበላ አብያተክርስቲያናት እና በሌሎች ታሪካዊ፣ ባሕላዊ እና ሃይማኖታዊ የቱሪዝም መዳረሻዎች ጎብኝዎችን የሚያስተናግድ፣ የጎብኝዎች መዳረሻ ነው።

ሰው ሠራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች ከመደራረባቸው አስቀድሞ በአካባቢው የነበረው የቱሪዝም ፍሰት ከፍተኛ ነበር። ሰው ሠራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች ግን ከፍተኛ የቱሪዝም መዳረሻ የነበረውን አካባቢ ጎድቶት ቆይቷል።

በቅዱስ ላሊበላ የሚከበረው ታላቁ የልደት በዓል የአካባቢውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት እንደሚመልሰው ይጠበቃል።

የሰሜን ወሎ ዞን ባሕል እና ቱሪዝም መምሪያ ኀላፊ ገነት ሙሉጌታ በዞኑ አሽንድዬ፣ ሶለል፣ ልደት እና ጥምቀት በድምቀት እንደሚከበሩ ገልጸዋል።

የአካባቢው ቱሪዝም ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጀምሮ ጉዳት ደርሶበት መቆየቱንም ተናግረዋል። የሰሜኑ ጦርነት እና አሁን በክልሉ ያለው ግጭትም ቱሪዝሙን እንደጎዳው ነው የተናገሩት።

የተቀዛቀዘውን የቱሪዝም እንቅስቃሴ የሚያነቃቃውን የልደት በዓል በድምቀት ለማክበር መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል። ሰላም ወዳዱ ሕዝብ ልደትን በታላቅ ሥርዓት ለማክበር መዘጋጀቱንም ተናግረዋል።

የአገልግሎት አሰጣጡን ማሻሻል እና ሌሎች የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን መሥራታቸውን ገልጸዋል።

ሆቴሎች እንግዶችን ለመቀበል መዘጋጀታቸውንም አመላክተዋል። የላሊበላ ሕዝብ የእንግዶችን እግር አጥቦ እና አክብሮ የሚቀበል መኾኑን ነው የተናገሩት። እንግዶች ቆይታቸው የተመቸ እንዲኾን ሥራዎች እየተሠሩ መኾናቸውንም ገልጸዋል።

እንግዶች በስፋት እንዲመጡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምቹ ኹኔታን እየፈጠረ መኾኑንም ተናግረዋል። እንግዶችም በዓሉን ለማክበር ወደ ላሊበላ እየገቡ መኾናቸውን ነው የገለጹት።

የልደት በዓል በችግር ውስጥ የቆዬውን አካባቢ እንደሚያነቃቃም ተናግረዋል። የላሊበላ ሕዝብ ምርት ቱሪዝም ነው ያሉት ኀላፊዋ በልደት እና በጥምቀት በዓል ገቢ የሚሠበሠብ መኾኑን ገልጸዋል። ቱሪዝም ለላሊበላ ትልቁ እና ዋናው የኢኮኖሚ ምንጭ ነው ብለዋል።

ከበዓሉ በኋላም የቱሪዝም እንቅስቃሴው እንደሚቀጥል ተስፋ ይደረጋል ነው ያሉት። የቱሪዝም እንቅስቃሴው ወደነበረበት እንደሚመለስ ያላቸውን ዕምነትም ገልጸዋል።

የቱሪዝም እንቅስቃሴው ከበዓል ማግሥትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል የአግልግሎት አሰጣጡን የተሻለ ማድረግ እና በጋራ መሥራት እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።

ቱሪዝም ስኬታማ እንዲኾን ሰላምን ማረጋገጥ እንደሚገባ ነው የተናገሩት። ማኅበረሰቡ ከመንግሥት ጋር በጋራ በመሥራት ሰላሙን መጠበቅ እንዳለበትም አሳስበዋል። ጎብኝዎች ወደ ታላቁ ሥፋራ እንዲመጡም ጥሪ ማቅረባቸውን ከአሚኮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

"የልደት በዓል ለላሊበላ የቱሪዝም እንቅስቃሴ ፋይዳው ከፍ ያለ ነው" የቅዱስ ላሊበላ እና አካባቢው ቱሪስት አስጎብኝ ማኅበር ***ዓለም አቀፉ እና ሀገር አቀፍ አስጎብኝዎች የቅዱስ ላሊበላ አ...
03/01/2025

"የልደት በዓል ለላሊበላ የቱሪዝም እንቅስቃሴ ፋይዳው ከፍ ያለ ነው" የቅዱስ ላሊበላ እና አካባቢው ቱሪስት አስጎብኝ ማኅበር
***
ዓለም አቀፉ እና ሀገር አቀፍ አስጎብኝዎች የቅዱስ ላሊበላ አብያተክርስቲያናትን እና የአካባቢውን ቅርሶች ለመጎብኘት በስፋት ይመጣሉ።

አምሳያ የሌላቸው የላሊበላ አብያተክርስቲያናት የጎብኝዎችን ቀልብ በመሳብ የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንዲያድግ ያላቸው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ ነው። በተለይም የልደት በዓል ሲደርስ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ጎብኝዎች ወደ ላሊበላ በብዛት ይመጣሉ።

አስጎብኝዎች እና ሌሎች ደግሞ ከቱሪዝም ተጠቃሚዎች ይኾናሉ። የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓልን ለማክበር እንግዶች እየገቡ ነው። በዚህ በዓል ደግሞ በርካታ እንግዶች የሚገኙበት በመኾኑ የቱሪዝም እንቅስቃሴውን ከፍ ያደርገዋል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።

የቅዱስ ላሊበላ እና አካባቢው ቱሪስት አስጎብኝ ማኅበር ሊቀመንበር እስታሉ ቀለሙ የቅዱስ ላሊበላ አብያተክርስቲያናት ሃይማኖታዊ፣ ታሪካዊ እና ባሕላዊ ትሩፋት ያላቸው በመኾናቸው በርካታ እንግዶች እየመጡ ይጎበኟቸዋል ብለዋል።

የልደት በዓል ደግሞ ለላሊበላ እና አካባቢው የቱሪዝም እንቅስቃሴ ያለው ፋይዳ ከፍ ያለ ነው ብለዋል። ለዓመታት በርካታ እንግዶች በረከትን ለማግኘት የልደትን በዓል በላሊበላ ሲያከብሩ መኖራቸውንም አስታውሰዋል።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት በተፈጠሩ ሰው ሠራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች ምክንያት የጎብኝዎች ቁጥር ቀንሶ እንደነበርም አንስተዋል። ፈውስ እና በረከትን ለማግኘት የሚሹ እንግዶች ረጅም ርቀትን ተጉዘው ወደ ላሊበላ መግባታቸውንም ገልጸዋል።

በዓሉ የበለጠ በቀረበ ቁጥር እንግዶች በስፋት እንደሚመጡ ይጠበቃል ነው ያሉት። 165 የሚደርሱ የላሊበላ እና አካባቢው አስጎብኝዎች የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን እና የአካባቢውን ድንቅ ታሪክ ለማስጎብኝት ዝግጁ መኾናቸውን ገልጸዋል። በሙያቸው ሀገራቸውን፣ ባሕላቸውን እና ታሪካቸውን በተገቢው መንገድ ለእንግዶች እንደሚያስተዋውቁም ተናግረዋል።

ቅርሱን ለማስተዋወቅ በቂ ዝግጅት መደረጉንም አመላክተዋል። የላሊበላ እና አካባቢው የቱሪዝም እንቅስቃሴ በልደት በዓል ብቻ ሳይኾን በሌሎች ጊዜያትም በጥሩ ሁኔታ እንዲቀጥል የአካባቢውን ሰላም አስተማማኝ ማድረግ ይገባል ነው ያሉት። ቱሪዝም ፍጹም ሰላም እንደሚፈልግም ገልጸዋል። ሰላም ከተረጋገጠ በኋላ እንግዶች ወደ አካባቢው እንዲመጡ ለማድረግ መቀስቀስ እንደሚገባም አመላክተዋል።

የቅዱስ ላሊበላ እና አካባቢው አስጎብኝዎች ታሪኩን እና ሃይማኖታዊ ሥፍራዎችን ለማስተዋወቅ ብቁ አቅም እንደላቸው ነው የተናገሩት። ባለፉት ዓመታት ሀገራቸውን በተገቢው መንገድ ሲያስተዋውቁ መቆየታቸውንም ተናግረዋል።

ጎብኝዎች ድንቅ የኾኑ የቅዱስ ላሊበላ አብያተክርስቲያናትን እና በአካባቢው ያሉ ሃይማኖታዊ እና ታሪካዊ ሥፍራዎችን እንዲጎበኙም ጥሪ አቅርበዋል። ታይቶ የማይጠገበውን ቦታ፣ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን እንዲያዩ እና በረከት እንዲያገኙም ጥሪ እናቀርባለን ነው ያሉት።

የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል እና በሚገባ ለማስተናገድ ዝግጁ መኾናቸውንም ተናግረዋል። የቱሪዝም እንዱስትሪው ከፍ እንዲል በትብብር መሥራት እንደሚገባም አመላክተዋል።
አሚኮ

የባህል አልባሳት ዲዛይነሮች ውድድር ማስታዎቂያ***የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ 16ኛውን የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በጎንደር ከተማ በጥር ወር በተለያዩ ዝግጅቶት በድምቀት ያካሂዳል፡...
02/01/2025

የባህል አልባሳት ዲዛይነሮች ውድድር ማስታዎቂያ
***
የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ 16ኛውን የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በጎንደር ከተማ በጥር ወር በተለያዩ ዝግጅቶት በድምቀት ያካሂዳል፡፡

በፌስቲቫሉ ከሚቀርቡ ዝግጅቶች መካከል አንዱ የባህል አልባሳት ዲዛይነሮች ውድድር ነው፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የቀረቡትን መስፈርቶች የምታሟሉ ግለሰቦች ወይም ማህበራት በውድድሩ እንድትሳተፉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

የመወዳደሪያ መስፈርቶች
❶ በአማራ ክልል የሚለበሱ (የሴት እና የወንድ) አልባሳት ቢያንስ 5 ዓይነት ማቅረብ የሚችል፣
❷ የባህል አልባሳት ይዘታቸውን ሳይቀይር አዘምኖ ማቅረብ የሚችል፣
❸ ከፈትል(ጥጥ) የተሰሩ አልባሳትን ሥራ ላይ ትኩረት አድርጎ የሰራ፣
❹ የባህል አልባሳትን ትዕይንት ለማሳየት የሚሆኑ ወንድና ሴት ሞዴሎች ያሉት እና ወጫቸውን ሸፍኖ በውድድሩ መቅረብ የሚችል፣
❺ ሁለት አዲስ ፈጠራን የሚያሳዩ አልባሳትን ማቅረብ የሚችል፣
❻ የባህል አልባሳት እውቀት ያለው እና መግለጽ የሚችል

🏆የቅድመ ማጣሪያውን በማለፍ በጎንደር ከተማ በሚካሄደው ውድድር አሸናፊ የሚሆን ዲዛይነር አማራ ክልልን በመወከል በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የባህል አልባሳት ዲዛይነር ውድድር የሚሳተፍ ይሆናል።
የምዝገባ ቦታ
📍ባህልና ቱሪዝም ቢሮ - ቢሮ ቁጥር 405 በአካል ወይም በውስጥ መልዕክት በመላክ ይመዝገቡ!
🗓የመመዝገቢያ ጊዜ ከታህሳስ 18 – 28/2017 ዓ/ም
☎️ለበለጠ መረጃ +251582209423

“ውጤታማ ተቋማዊ አሰራርን ለመተግበር በየደረጃው ያለውን ፈጻሚና አስፈጻሚ አቅም ማጎልበት ያስፈልጋል” የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ ********(ታህሳስ 24/...
02/01/2025

“ውጤታማ ተቋማዊ አሰራርን ለመተግበር በየደረጃው ያለውን ፈጻሚና አስፈጻሚ አቅም ማጎልበት ያስፈልጋል” የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ም/ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ
********
(ታህሳስ 24/2017 ዓ.ም አብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ) በአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በዛሬው ዕለት በተሻሻለው የሰው ሃብት ምልመላ መረጣ መመሪያ እና በለውጥ አመራር አደረጃጀት ዙሪያ ለቢሮው ሰራተኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

በስልጠናው ላይ የተገኙት የቢሮው ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ “ውጤታማ ተቋማዊ አሰራርን ለመተግበር በየደረጃው ያለውን ፈጻሚና አስፈጻሚ አቅም ማጎልበት ያስፈልጋል” ብለዋል፡፡

አንድ ተቋም ውጤታማ የሚሆነው ተቋማዊ ዕቅድ ከማቀድ ጀምሮ እስከ ሰው ሃብት ስምሪት ድረስ እንዲሁም ልዩ ልዩ የክትትልና ግምገማ ስርዓቶችን መተግበር ሲቻል ነው ያሉት አቶ አባይ እነዚህ ተግባራት ውጤታማ የሚሆኑት ደግሞ በእውቀትና በክህሎት መተግበርና መምራት ሲቻል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ለዚህም ተከታታይና ወቅታዊ የሆነ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን ማመቻቸት አንዱ ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን አቶ አባይ ገልጸዋል፡፡ የተቋሙ ሰራተኛም በየጊዜው የሚሰጡ ስልጠናዎችን በአግባቡ መከታተልና መተግበር ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በየደረጃው የሚወጡ መመሪያዎችንና አሰራሮችን በተገቢው መንገድ አውቆ እና ተገንዝቦ በቅንነትና በታማኝነት አገልግሎት መስጠት እንደሚገባም አቶ አባይ አስገንዝበዋል፡፡

ስልጠናውን ከአብክመ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የመጡት አቶ ናትናዔል ሙጨ እና አቶ አዳምጠው አሻግሬ እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

ስልጠናው በነገው ዕለትም የሚቀጥል ይሆናል፡፡

"ላሊበላ ልዩ ቅርስ ነው፤ ኢትዮጵያም ልዩ ሀገር ናት" ከታይዋን የመጡ ጎብኝ****በድንቅ ጥበብ የታነጹት የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት የጎብኝዎችን ትኩረት ይስባሉ። ዓለም አቀፍ ጎብኝዎ...
02/01/2025

"ላሊበላ ልዩ ቅርስ ነው፤ ኢትዮጵያም ልዩ ሀገር ናት" ከታይዋን የመጡ ጎብኝ
****
በድንቅ ጥበብ የታነጹት የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት የጎብኝዎችን ትኩረት ይስባሉ። ዓለም አቀፍ ጎብኝዎች ከኢትዮጵያ ውጭ የማይታዩትን ድንቅ አብያተክርስቲያናት ለማየት ከሩቅ ተጉዘው ይመጣሉ።

የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን እየጎበኙ ያገኘናቸው ከታይዋን የመጡ ጎብኝዎች ባዩት ነገር መደነቃቸውን ነግረውናል። የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት ልዩ እና ድንቅ መኾናቸውንም ገልጸዋል።

ከአሚኮ ጋር ቆይታ ያደረጉት ሊ ሁ የህ "ወደ ላሊበላ ስመጣ ለመጀመሪያ ነው፤ ውብ ምድር እና ውብ ሀገር አይቻለሁ" ብለዋል።

የላሊበላ የኪነ ሕንጻ ጥበቡ የሚደንቅ መኾኑን ነው የገለጹት። ሕዝቡም ደግ መኾኑን ተናግረዋል። በቆይታቸው እንጀራ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ምግቦች እንደተመቻቸውም ገልጸዋል። በላሊበላ ባዩት ነገር ሁሉ እየተደሰቱበት መኾኑንም ተናግረዋል።

ከአሥር ጊዜ በላይ የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናትን የጎበኙት ሮቦርት ሁዋንግ በተደጋጋሚ ባዩት ቁጥር እንደሚደነቁበት ነው የገለጹት።

የላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት ብቻ ሳይኾኑ በሥፍራው ያሉ አማኞች ኅብረ ዝማሬም የሚገርም መኾኑን ተናግረዋል።

መንፈሳዊ ሥርዓቱ እና የአብያተ ክርስቲያናቱ አሠራር የሚደንቅ መኾኑን ገልጸዋል። በመላው ዓለም የሚገኙ ጎብኝዎች ላሊበላን እንዲጎበኙ እና የልደት በዓልን በላሊበላ እንዲያከብሩ ጥሪ አቀርብላቸዋለሁ ነው ያሉት።

የልደት በዓል አከባበር በኢትዮጵያ ከሌሎች ዓለማት ሁሉ የተለየ እና ድንቅ ነው ያሉት ሁዋንግ የኢትዮጵያ የልደት በዓል አከባበር ከምዕራባውያን እና ከሌሎች ዓለማት ሁሉ የተለየ እና የሚደንቅ ነው ብለዋል።

ሌላኛዋ ጎብኚ ሊ ሺ ቺያ ሊን "ድንቅ የኾኑ አብያተክርስቲያናት እና ጥልቅ የኾነ ሃይማኖታዊ ሥርዓት ተመልክቻለሁ" ነው ያሉት።

ከመምጣቴ አስቀድሞ ስለ ኢትዮጵያ ስሰማው የነበረው እና መጥቼ ያየሁት ፈጽሞ አይገናኝም ብለዋል። እርሳቸው ከመምጣታቸው አስቀድሞ በአዕምሯቸው የነበረችው ኢትዮጵያ ደሀ እና ሕዝቦቿም በችግር ውስጥ የሚኖሩ እንደኾኑ ያስቡ እንደነበር ነው የተናገሩት። ከመጡ በኋላ ያዩት ነገር ግን የሚደነቅ መኾኑን ነው የገለጹት።

መጥቼ ካየሁት በኋላ ግን ጥንታዊ ባሕል፣ ሃይማኖት እና ቅርስ ያላቸው መኾናቸውን አይቻለሁ ብለዋል። የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢን ጎብኝተው እንደመጡም ተናግረዋል፡፡

ጎብኝዋ በደቡብ አካባቢ የሚደንቅ ባሕላዊ ሥርዓት አለ፣ ወደ ሰሜኑ ክፍል ደግሞ ቅርስ እና ታሪካዊ ሥፍራዎች እንደሚበዙ ተመልክቻለሁ ነው ያሉት።

ስለ ኢየሱስ እና ስለ ቤተክርስቲያን መምህሬ በስፋት ነግሮኛል፣ በላሊበላ ያሉ አብያተክርስቲያናት እና ሃይማኖታዊ ሥርዓት ግን በየትኛውም ዓለም የሌሉ ናቸው ብለዋል። ባየሁት ነገር እጅግ ተደንቄያለሁ ነው ያሉት።

ዓለም አቀፍ ጎብኝዎች ወደ ኢትዮጵያ ቢመጡ ብዙ ነገር ያተርፋሉ፣ እኛ እንዳየነው አይነት የሚያስገርም ሥራ ማየት ይችላሉ ብለዋል። ሕዝቡም የሚገርም ነው። ጎብኝዎች ወደ ኢትዮጵያ ኑ ነው ያሉት።

እንደ ላሊበላ አይነት ቅርስ በየትኛውም ዓለም የለም፣ ይሄ ልዩ ቅርስ ነው፣ ኢትዮጵያም ልዩ ሀገር ናት ነው ያሉት።

በላሊበላ የሚደንቅ መንፈሳዊ ሥርዓት ነው ያለው፣ በኢትዮጵያ ያለው ባሕል እና ሃይማኖት እጅግ የሚደነቅ ነው ብለዋል።
አሚኮ

የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ እየተካሄደ ነው ****አስራስድሥተኛው የባሕል እና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ እየተካሄደ ነው። ፌ...
02/01/2025

የባህልና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ እየተካሄደ ነው
****
አስራስድሥተኛው የባሕል እና ኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ እየተካሄደ ነው።

ፌስቲቫሉ የባህል ትውውቅን ከመፍጠር አኳያ ጉልህ ሚና እንዳለው ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል።

ኪነ-ጥበብ የማኅበረሰብን ወግ እና ባሕል ከማስተዋወቅ አንጻር የማይተካ ሚና እንዳለውም ተገልጿል።

የሰሜን ጎንደር ዞን ተወካይ አሥተዳዳሪ አደራጀው ባዘዘው ባሕል እና ወግን ጠብቆ ለቀጣይ ትውልድ ለማስተላለፍ እና ማኅበራዊ እሴቶችን ለማጎልበት ኪነ-ጥበብ ሚናው ከፍተኛ ነው ብለዋል።

የባሕል እና ኪነ-ጥበብ ዓውደ ርዕይ ተተኪ ከያኒያንን ለማፍራት እና ለማበረታታት ቁልፍ መንገድ ነው ያሉት ደግሞ የሰሜን ጎንደር ዞን ባሕል እና ቱሪዝም መምሪያ ኀላፊ ወ/ሮ አስራት ክብረት ናቸው።

በዓውደ ርዕዩ ለመሳተፍ ከተለያየ አካባቢዎች የመጡ የባሕል ቡድን አባላት፣ እርስ በርስ ለመተዋወቅ እና ልምድ ለመቅሰም እንዳገዛቸው ገልጸዋል።

በዓውደ ርዕዩ ላይ ከዞኑ ወረዳዎች የተወጣጡ የባሕል ቡድኖች እና ተጋባዥ እንግዶች ተሳታፊ መሆናቸው ተገልጿል።

አባቶቻችን ያስቀመጡልንን ሥርዓት እንጠብቃለን" የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም አስተዳዳሪ አባ ሕርያቆስ  ጸጋዬ ****ላሊበላ እንግዶቿን እግር እያጠበች መቀበሏን ቀጥላለች።  የደብረ ሮሐ ...
02/01/2025

አባቶቻችን ያስቀመጡልንን ሥርዓት እንጠብቃለን" የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም አስተዳዳሪ አባ ሕርያቆስ ጸጋዬ
****
ላሊበላ እንግዶቿን እግር እያጠበች መቀበሏን ቀጥላለች። የደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ መነኮሳት፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና የከተማዋ ነዋሪዎች እንግዶችን እግር እያጠቡ በመቀበል ተጠምደዋል።

ሁሉም በረከት ለማግኘት ሲፋጠኑ ይውላሉ። የእንግዶችን ጓዝ እየተቀበሉ በጥላ ያሳርፋሉ። ከእግራቸው ሥር ኾነው እግር ያጥባሉ። አክብሮትም ይሰጣሉ። በረከት አይለፈኝ በሚል ያለው እሽቅድምድም ቀጥሏል።

እንግዶችን ዝቅ ብለው እግር በማጠብ የሚቀበሉት የደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ገዳም አሥተዳዳሪ አባ ሕርያቆስ ጸጋዬ አባቶቻችን የልደትን በዓል በላሊበላ ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን እግር እያጠቡ ሲቀበሉ ኖረዋል ነው ያሉት። እኛም አባቶቻችን ያስቀመጡልንን ሥርዓት እና ያስረከቡንን ትውፊት ለመጠበቅ ኀላፊነት እና አደራ አለብን ብለዋል። አባቶቻችን ያስቀመጡልንን ሥርዓት እንጠብቃለን ነው ያሉት።

እግር በማጠብ ትህትናን ያስተማረን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ብለዋል አባ ሕርያቆስ። ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር የነበረውን የወንጌል አገልግሎት ፈጽሞ የመጨረሻው ራት ጊዜ ያደረገው በትህትና ዝቅ ብሎ የሐዋርያትን እግር ማጠብ ነበር ነው ያሉት።

እግር ማጠብ የትህትና ምልክት ነው ያሉት አባ ሕርያቆስ መንፈሳዊ ሥራዎች ከሚገለጡባቸው ተግባራት መካከል አንደኛው መኾኑንም ገልጸዋል። ጌታ ተንበርክኮ የሐዋርያትን እግር አጥቧል፣ ካጠባቸውም በኋላ እናንተም ለባልንጀራችሁ አድርጉት ብሎ ትዕዛዝ ሰጠ ብለዋል። ቤተክርስቲያንም ቃሉን እና ትዕዛዙን መሠረት አድርጋ እግር እያጠበች ተገቢውን የእንግዳ አቀባበል ሥርዓት ትፈጽማለች ነው ያሉት። እኛም ቤተክርስቲያን ባስተማረችን፣ ጌታችን ባዘዘን እና አባቶቻችን ባቆዩን ሥርዓት መሠረት እግር እናጥባለን ብለዋል።

ከፍቅር ሁሉ የሚቀድመው ባልንጀራን መውደድ ነው ያሉት አባ ሕርያቆስ ከአባቶቻችን በተቀበልነው ሥርዓት እና ትውፊት መሠረት እንግዶቻችንን እግራቸውን እያጠብን ነው፣ ይሄንም ሥርዓት ለልጆቻችን እናስተላልፋለን ነው ያሉት።

የሚገቡ እንግዶችን እግር እያጠቡ እንኳን ደህና መጣችሁ የሚሉት የላሊበላ ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ወንድምነው ወዳጅ የቅዱስ ላሊበላ ሕዝብ እንደተለመደው ባማረ የእንግዳ አቀባበል ባሕል እንግዶችን እየተቀበለ ነው ብለዋል። በረከት ባለው እና ተስፋ በሚሰጥ ተግባር እየተሳተፉ መኾናቸውንም ገልጸዋል።

ስንጓጓለት የነበረው በዓል ደርሶ እንግዶችን እግር እያጠብን እየተቀበልን ነው ብለዋል። ዝቅ ብለን እግር እያጠብን እንግዶችን ለመቀበል ስለደረስን እና ስለበቃን ደስተኞች ነን ነው ያሉት። የእንግዳ አቀባበል እና ዝቅ ብሎ ማገልገል የቆዬ ባሕላቸው እና ትውፊታቸው መኾኑንም ገልጸዋል።

የእንግዳ አቀባበል ትውፊታችን እና በረከት የሚገኝበት ሥርዓታችን እንዲቀጥል ሰላምን ማስጠበቅ ወሳኝ ነው ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ልደት ደግሞ የሰላም፣ የፍቅር እና የበረከት በዓል ነው ብለዋል። የተወደደውን ባሕል እና ትውፊት ይዞ ለመዝለቅ ሰላም ላይ መሥራት እና የቆየውን ሥርዓት መጠበቅ እንደሚገባ ነው የተናገሩት።

የሰሜን ወሎ ዞን ባሕልና ቱሪዝም መምሪያ ኀላፊ ገነት ሙሉጌታ ለልደት በዓል ወደ ላሊበላ የሚገቡ እንግዶችን ባማረ የእንግዳ አቀባበል መቀበል የሚያስደስት መኾኑን ተናግረዋል። እግር እያጠቡ እንግዶችን መቀበል መልካም እና የቆየ እሴት መኾኑን ገልጸዋል ሲል የዘገበው አሚኮ ነው።

"በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቱሪዝም ለሰላም እና ብዝሃነት” በሚል መሪ ቃል የቱሪዝም ሳምንት እየተከበረ ነው ፡፡*******(ታህሳስ 23/2017ዓ.ም) በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ የቱሪ...
01/01/2025

"በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቱሪዝም ለሰላም እና ብዝሃነት” በሚል መሪ ቃል የቱሪዝም ሳምንት እየተከበረ ነው ፡፡
*******
(ታህሳስ 23/2017ዓ.ም) በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመጀመሪያ ጊዜ የቱሪዝም ሳምንት መከበር የተጀመረ ሲሆን የቱሪዝምና ሆቴል ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትና የስርዓተ ትምህርቱ አንዱ አካል መሆኑም ተገልጿል፡፡

የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት አዕምሮ ታደሰ(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ቱሪዝምን አንዱ የትኩረት መስክ በማድረግና የቱሪዝም እና ሆቴል ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል በመክፈት በዘርፉ የሰለጠኑ ሙያተኞችን በማፍራት የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን በማስተዋወቅና በማዘመን አካባቢውን፣ ክልሉን ብሎም ሀገሪቱን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር አዕምሮ አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው የቱሪዝም እና ማኔጅመንት ትምህርት ከማስተማር በተጨማሪ በዘርፉ ብቃት ያላቸውን ሙያተኞች ለማፍራት የሚያስችል የቱሪዝም እና ሆቴል ማሰልጠኛ እና ምዘና ማዕከል በማቋቋም ወደ ስራ እንዲገባ መደረጉን ገልጸው ማዕከሉን በስልጠና ለማጠናከር ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ማሰልጠኛ ተቋም እና አማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር የመግባቢያ ሰነድ መፈራሩምንም አስታውሰዋል፡፡

ዛሬ የሚጀምረው የቱሪዝም ሳምንት ለትምህርት ክፍሉ ተማሪዎች የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበት እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው እና ማሕበረሰቡ ደግሞ ስለቱሪዝም ግንዛቤ ለመፍጠር ዓላማ ያለው በመሆኑ ይህ ሳምንታዊ የቱሪዝም ሳምንት በስርዓተ ትምህርቱ ውስጥ የተካተተ በመሆኑ በየዓመቱ በተመሳሳይ የሚከበርና ተጠናክሮ የሚቀጥል ተግባር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን የሆኑት ይልቃል አንዱዓለም(ዶ/ር) በበኩላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረው የቱሪዝም ሳምንት ኤግዝቢሽን፣ ጥናታዊ ጽሑፍ እና የምክክር መድረክ፣ ውዝዋዜ እና የድምጽ ውድድር፣ የእግር ጉዞ እና የፈረስ ባህላዊ ትርዒት ያካተተ መርሐ ግብር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ የተገኙት የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ሃላፊ ለይኩን ሲሳይ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለቱሪዝም እና ሆቴል ማኔጅመንት በሠጠው ትኩረት በተለይም የቱሪዝም እና ሆቴል ማሰልጠኛ እና ምዘና ማዕከል በመክፈት ብቁ የሰው ሀይል ለማፍራት ለሚያደርገው ከፍተኛ አስተዋጽኦ አመስግነዋል፡፡

በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች እና የሴኔት አባላት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንዲሁም ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ Injibara University

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከባህርዳር ላሊበላ ቀጥታ በረራ ሊጀምር ነው!==========================የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ  ታህሳስ 28/2017 ዓም ከባህርዳር - ላሊበ...
01/01/2025

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከባህርዳር ላሊበላ ቀጥታ በረራ ሊጀምር ነው!
==========================
የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ታህሳስ 28/2017 ዓም ከባህርዳር - ላሊበላ ቀጥታ በረራ የሚሰጥ ሲሆን ታህሳስ 29/2017 ዓም ደግሞ ከላሊበላ- ባህርዳር ቀጥታ በረራ የሚሰጥ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።

"እንግዶችን እየተቀበልን ነው" የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት*****በታላቁ ሥፍራ በዓሉን ለማክበር ቀደም ብለው የተነሱ እንግዶች ላሊበላ ደርሰዋል።  ላሊበላ ያልደረሱት ...
01/01/2025

"እንግዶችን እየተቀበልን ነው" የላሊበላ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
*****
በታላቁ ሥፍራ በዓሉን ለማክበር ቀደም ብለው የተነሱ እንግዶች ላሊበላ ደርሰዋል። ላሊበላ ያልደረሱት ደግሞ በጉጉት እየተጠበቁ ነው።

የላሊበላ ከተማ አሥተዳደር እና የከተማዋ ነዋሪዎችም አስቀድመው ዝግጅታቸውን አጠናቅቀው እንግዶችን እየተቀበሉ ነው።

የላሊበላ ከተማ አሥተዳደር ባሕል እና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ዲያቆን አዲሴ ደምሴ የልደት በዓልን ለማክበር ልዩ ልዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አከናውነን ጨርሰናል ብለዋል። አሁን ላይ እንግዶችን እየተቀበሉ መኾናቸውንም ገልጸዋል።

እንግዶች የሚያርፉባቸው ሆቴሎች እና ሌሎች አማራጮችን ማዘጋጀታቸውንም ተናግረዋል። እንግዶች በሆቴሎች እና በቤተክርስቲያን አጸድ ሥር እንደሚያርፉም ገልጸዋል። የሚመጡ እንግዶች የማረፊያ ችግር አይገጥማቸውም ብለዋል።

የከተማዋ ወጣቶች እየገቡ ያሉ እንግዶችን እግር እያጠቡ እየተቀበሏቸው ነው። በከተማዋ ያሉ እድሮች እንጀራ እያዋጡ ለእንግዶች እያቀረቡ መኾናቸውን ገልጸዋል። የበዓሉ ቀንም እንግዶችን ጾም እያስፈቱ እንደሚሸኟቸው ነው የተናገሩት።

የቅዱስ ላሊበላ አብያተክርስቲያናት በኢትዮጵያ ግንባር ቀደም የቱሪዝም መዳረሻ መኾናቸውን የተናገሩት ኀላፊው ከተማዋ የዓለምን ቅርስ የያዘች የዓለም ከተማ መኾኗንም ገልጸዋል።

የከተማዋ ነዋሪዎች የገቢ ምንጫቸው ቱሪዝም መኾኑንም አንስተዋል። የልደት በዓል ከፍተኛ የቱሪዝም መነቃቃት እንደሚፈጥርም ገልጸዋል።

የከተማዋ ነዋሪዎች የዓመት ልብሳቸውን እና ጉርሳቸውን የሚያገኙት ከልደት በዓል ላይ መኾኑን ነው የተናገሩት። የልደት በዓል ከሃይማኖታዊ በዓልነቱ ባሻገር ለላሊበላ ከተማ ልዩ ትርጉም አለው ነው ያሉት።

የከተማዋ ነዋሪዎች የልደትን በዓል በጉጉት እንደሚጠብቁትም ገልጸዋል። በችግር ውስጥ የቆዬውን ቱሪዝም ለመመለስ በዓሉን በድምቀት ማክበር ትልቅ ፋይዳ አለው ነው ያሉት።

ከበዓሉ በኋላም የሀገር ውስጥ እና የውጭ ጎብኝዎች ላሊበላን እንዲጎበኙ እየሠሩ መኾናቸውንም ገልጸዋል። ባሕላዊ እና ሃይማኖታዊ በዓላትን በድምቀት ማክበር ለቱሪዝም ዕድገት ፋይዳው ከፍተኛ መሆኑን ኃላፊው መግለጻቸውን ከአሚኮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

በአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ መስተንግዶ አሰጣጥ ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡*******የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከኢትዮጵያ ቱሪዝምና ሆቴሎች ማርኬቲንግ ማህበር...
01/01/2025

በአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ መስተንግዶ አሰጣጥ ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
*******
የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከኢትዮጵያ ቱሪዝምና ሆቴሎች ማርኬቲንግ ማህበር ጋር በመተባበር በባህርዳር ከተማ ለሚገኙ የሆቴልና ቱሪዝም መስተንግዶ ሰራተኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

በዛሬው ዕለት በተጀመረው ስልጠና ላይ ከባህር ዳር፣ ዘጌ እና ጭስ አባይ አስጎብኝ ማህበራት ተወካዮች፣ የሆቴል ስራ ክፍል ሃላፊዎችና የሆቴሎች ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡

ስልጠናው በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ የማርኬቲንግ ስራ፣ በጉብኝትና መስተንግዶ ዘርፍ የእንግዳ አቀባበልና አያያዝ በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ነው ስልጠናው እየተሰጠ የሚገኘው፡፡

በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ የመስተንግዶ ዘርፍ ውስንነት የሚስተዋልበትና ቅልጥፍና የሚጎድለው የአገልግሎት አሰጣጥ ችግር መኖሩን ተናግረዋል፡፡

ለቱሪዝም ዘርፍ ቀልጣፋና ጥራት ያለው የመስተንግዶ አሰጣጥ አንዱ ቁልፍ ጉዳይ መሆኑን አንስተው ዓለም ዓቀፍ ተወዳዳሪ ለመሆንና ቱሪስቶችን ቆይታ ለማራዘምም በሆቴልና ቱሪዝም ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት ደንበኞችን ማርካት ይጠበቃል ብለዋል፡፡

የተዘጋጀው ስልጠናም በዘርፉ የደምበኞች አያያዝና የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን አቅም የሚፈጥር መሆኑን አስገንዝበው ሰልጣኞች ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል በየሆቴሎቻቸው ዘርፉ የሚጠይቀውን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የተዘጋጀው ስልጠና ለሁለት ቀን የሚቆይ ሲሆን የሆቴሎች ሰራተኞችም እንደሚሳተፉ ለማዎቅ ተችሏል፡፡

ለልደት በዓል ዝግጅት በላሊበላ  ...አሁናዊ ገጽታ****ልደትን ለማክበር እንግዶች ወደ ላሊበላ መግባት ጀምረዋል ። እንደወትሮው ሁሉ ላሊበላ እንግዶቿን ልዮ በሆነው የእግር አጠባ በማካሄድ ...
31/12/2024

ለልደት በዓል ዝግጅት በላሊበላ ...አሁናዊ ገጽታ
****
ልደትን ለማክበር እንግዶች ወደ ላሊበላ መግባት ጀምረዋል ። እንደወትሮው ሁሉ ላሊበላ እንግዶቿን ልዮ በሆነው የእግር አጠባ በማካሄድ እየተቀበለች ነው።
ገናን በላሊበላ ያክብሩ!!
#ቤዛኩሉ #ገና #ላሊበላ

በኪነ-ህንፃ ጥበቡ አለምን ያስደነቀው የላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስትያናት አሁን ላይ ደግሞ ልዩ በሆነው የቤዛ-ኩሉ ስነ ስርዓት ዳግም አለምን ያስደምማል፣ የገና ዕለት ደምቆ ይውላል። ይህን ...
31/12/2024

በኪነ-ህንፃ ጥበቡ አለምን ያስደነቀው የላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስትያናት አሁን ላይ ደግሞ ልዩ በሆነው የቤዛ-ኩሉ ስነ ስርዓት ዳግም አለምን ያስደምማል፣ የገና ዕለት ደምቆ ይውላል።

ይህን አስደማሚ በዓል በቦታው ተገኝተው ይታደሙ!!
ገናን በላሊበላ ያክብሩ!!
#ቤዛኩሉ #ገና #ላሊበላ

በቀጣይ ወራት በሚከበሩ በዓላት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ*****የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ተጠሪ ጽ/ቤት በከተማው በወርሃ ጥር የሚከበሩ በዓላትን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት...
31/12/2024

በቀጣይ ወራት በሚከበሩ በዓላት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ
*****
የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ተጠሪ ጽ/ቤት በከተማው በወርሃ ጥር የሚከበሩ በዓላትን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።

በውይይቱ መክፈቻ ያደረጉት የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ደሴ መኮንን እንደገለጹት በከተማው ታህሳስ 29 ቀን የሚከበረውን የገና/ልደት በዓልን ጨምሮ ወርሃ ጥር ለደብረታቦር ከተማና አካባቢው ልዩ ድምቀት የሚሰጥ በመሆኑ ወቅቱን ለቱሪዝም የተመቻቸ ማድረግና አካባቢውን በሚገባው ልክ እንዲለማ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

የቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎችን ማልማትና ለቱሪዝም ምቹ ማድረግ ላይ በትኩረት ተይዞ በትብብር መስራት እንደሚገባም ከንቲባው ገልጸዋል።

በመድረኩ የመወያያ ሀሳብ ያቀረቡት የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ተጠሪ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አሉበል ደመላሽ እንደገለጹት ቱሪዝም የአለም የኢኮኖሚ ሞተር መሆኑን እና እንደ ኢትዮጵያም በርካታ የቱሪዝም ሀብቶች የሚገኙ መሆኑን አንስተዋል።

እንደ ደብረታቦር ከተማ ተጨባጭ ሁኔታም በርካታ የሚዳሰሱና የማይዳሰሱ ታሪካዊ፣ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ የመስህብ ሀብቶች እንደሚገኙና ከእነዚህም ውስጥ ወርሃ ጥርን የሚያደምቁት በዓላት ገና፣ ጥምቀት፣አስተርዮና መርቆሪዎስ ለከተማው ድምቀት እንደሆኑ ገልጸዋል።

በፈረስ ጉግስ የሚደምቀውን የመርቆሪዎስ በዓል በድምቀት ለማክበርም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።

በወርሃ ጥር በተለይም በፈረስ ጉግስ ውድድርና በሽምጥ ግልቢያ እንዲሁም በልዩ ልዩ መንፈሳዊ እና ባህላዊ ክንዋኔዎች የሚደምቀው የመርቆሪዎስ በዓልን በሚገባው ልክ ለማሳደግና በቱርዝም ዘርፍ ከተማውና ማህበረሰቡ እንዲጠቀም ባለድርሻ አካላት በትብብር መስራት እንደሚገባም ተመላክቷል።

በቀጣይ የሚከበሩ በዓላትን በደምቀት ለማክበር ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ አቅጣጫ መቀመጡንም ከደብረ ታቦር ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Culture & Tourism Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share