Sahibu Page

Sahibu Page AdisAbeba

28/01/2023

አዲስ የተቋቋመው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ 12 የነባሩን ሲኖዶስ አባላት አወገዘ።

እነዚህ ጳጳሳት ከዲቆንነት ጀምሮ እስከ ሊቀ ጳጳስነት የተሰጣቸው የክህነት ማእረግ እንዲነሳና ከዚህ በኋላ አቶ በሚለው ማእረግ እንዲጠሩ ወስኗል።

የነባሩ ሲኖዶስ አካሄድ ምእመናንና ቤተክርስቲያኗ የሚጠቅም አይደለም፣ የአንድ ቡድንና ወገን መገልገያ ሆኗል ብሏል።

የአዲሱ ሲኖዶስ አባላት ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጡት መግለጫ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት በሚከተለው አንድ ሀገር፣ አንድ ቋንቋ ፖሊሲ በገዢው መደብና በቤተ ክርስቲያን አለቆች ስምምነት ከግዕዝና ከአማርኛ ቋንቋ በቀር ቤተክርስቲያንን ለማገልገል ሳይፈቀድ መቆየቱን አስታውሰዋል።

ይህም የሆነው ከአንድ ጎሳ የሚወለዱ የቤተ መንግሥትና የቤተ ክህነት ገዥዎችን የጥቅም ክፍፍል ለማስቀጠል መሆኑን አስረድተዋል።

በመሆኑም ባለፉት ሰባ ዓመታት የተደራጀው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነትና የጳጳሳት ሹመት የወንጌል አገልግሎት ለብሔር ብሄረሰቦች በቋንቋቸው ማድረስ ሳይሆን በአብዛኛው የበለጠ ሥጋዊ ሀብትን ለማደላደል በሚፈልጉ ኤጵስቆጶሳት እየተሞላች መምጣቷን ተናግረዋል።

ቀስ በቀስ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ምእመናንን ለቤተ ክርስቲያናቸው እንግዳ እንዲሆኑና ከቤተ ክርስቲያን እንዲርቁ እያደረገ መምጣቱንም አክለዋል።

ይህንን ችግር መፍታት ያልቻለው ነባሩ ሲኖዶስ ይህንን ችግር ለመፍታት እየተጉ ያሉት ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳትና 25-ቱ ኤጲስ ቆጶሳት ላይ ያስተላለፈው ውሳኔ ለቤተ ክርስቲያን የሚቆረቆሩና ለቤተ ክርስቲያን የሚተጉትን ካህናት፣ ዲያቆናትና ምእመናንን ከቤተ ክርስቲያን አርቆ በቤተ ክርስቲያን ውድቀት የተለመደ ሥጋዊ ምቾታቸውንና ጎጠኛ ፍላጎታቸውን ለመምራት እንዲመቻቸው ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።

እንዲሁም የአዲሱ ሲኖዶስ ዓላማ እንደ ከሳሾች የዘርና የጎሳ ክፍፍል ለመፍጠር ሳይሆን የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ነው ያሉ ሲሆን የተሾሙት አባቶችም ከሹመታቸው በፊት ቤተክርስቲያን በሰጠቻቸው ልዩ ልዩ ታላላቅ ኃላፊነቶችን ሲወጡ የነበሩና አገልግሎታቸውም በምእመናን ዘንድ የታወቀና የተመሰከረላቸው መሆኑን ጠቅሰዋል።

ከዚህም በላይ ነባሩ የሲኖዶስ አባላት ከቀኖና ውጪ የጵጵስና ሹመት ያደረጉ ሊቃነ ጳጳሳት እንዳሉ እያወቁ በጎጠኝነት ድጋፍ አድርገው በቀኖናው መሰረት የተሾሙትን ኤጲስ ቆጶሳት ማውገዝ ትርጉም የሌለውና እውነተኞች አባቶች ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ እንዳይገቡ ለመከላከል የተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

"እራሳቸው እንደገለጹት ውግዘት ካስተላለፉ በኋላ የችግሩን ምንጭ ለማጥናት ኮሚቴ እንዲቋቋም መወሰናቸው የማውገዝ ዓላማቸውን በቶሎ ለመፈጸም እንጂ ችግሩን በትክክል መርምሮ እልባት ለመስጠት አልነበረም" በማለትም አክለዋል።

የግብጽ ቤተክርስቲያን ጭምር አውግዛለች መባሉ ላይም "ለ1,600 ዓመታት ቤተ ክርስቲያናችን ከራሷ ልጆች ጳጳሳት ሹማ በሕዝቦችዋ ቋንቋ እንዳታስተምር ማድረጉዋ እየታወቀ፣ በእስራኤል ሀገር የሚገኘውን የዴር ሱልጣን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ገዳማችንን ለመንጠቅ የምትታገለንን እንደ ደጋፊና ተቆርቋሪ ቆጥሮ የኤጲስ ቆጶሳቱን ምርጫ ተቃወመች መባሉ ምእመናንን ለማሳሳትና ጥንቱንም የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እንዳትስፋፋ ያደረገችውን እንደ በጎ ተግባር መውሰድ ነው" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በልዩ ሁኔታ አሁን የተሰጠውን ሲመት በመቃወም፣ ለክፍፍል ምክንያት በመሆን፣ ቅዱስ ሲኖዶስን በማሳሳትና ሕዝበ ክርስቲያንን ግራ በማጋባት ላይ የተገኙት ያለውን 12 ጳጳሳትን ሲኖዶሱ ከሊቀ ጵጵስና እስከ ድቁና ያለውን ቤተ ክርስቲያን የሰጠቻቸውን ሥልጣነ ክህነት አንስቶ አውግዞ የለያቸው መሆኑንና ከዚህ በኋላ በቀደመ ዓለማዊ ስማቸው "አቶ" ተብለው እንዲጠሩ ምልዓተ ጉባኤው መወሰኑን አሳውቀዋል።

እነዚህም
አቡነ አብርሃም
አቡነ ጴጥሮስ
አቡነ ኤሊያስ
አቡነ ፋኑኤል
አቡነ ናትናኤል
አቡነ ዮሴፍ
አቡነ ዲዮስቆሮስ
አቡነ ሄኖክ
አቡነ መርቆርዮስ
አቡነ ሩፋኤል
አቡነ ሃሪያቆስ
አቡነ ኤሊያስ(ራሳቸውን በስዊድን ጳጳስ አድርገው የሾሙ) መሆናቸውን ሲኖዶሱ አስታውቋል።

በተጨማሪም ሌሎቹ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ይህን ቅዱስ ሲኖዶስ ለማውገዝ በጉባኤው የተገኙ አባላት ወደ ማስተዋል ተመልሰው እየፈጸሙ ያሉትን ቤተ ክርስትያንን የመክፈል ተግባራቸውን እንዲያጤኑም መክረዋል።

ይሁን እንጂ በያዙት አቋም በመጽናት ቤተክርስትያንን የመክፈል ዓላማቸው ላይ የሚጸኑ ከሆነ ከላይ በተጠቀሱት ግለሰቦች ላይ የተላለፈው ቃለ ውግዘት የሚተላለፍባቸውና በተሳሳተ አቋማቸው ምክንያት ለሚወሰድባቸው ቀኖናዊ እርምት ሃላፊነትን እንደሚወስዱ አሳስቧል።

የቤተ ክርስቲያንን ንብረት ለመጠበቅ ሲባልም በጊዜያዊነት ከዚህ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በኋላ ማናቸውንም በእጃቸው የሚገኙ የቤተክርስቲያንን ንብረትና ቅርሶች እንዲሁም ለአገልግሎት የሚውሉ ማናቸውንም ንዋየ ቅድሳት ከቦታ ወደ ቦታ እንዳያንቀሳቅሱና እንዳያሸሹ ምዕመናን እና በተለያየ እርከን ላይ ያሉ የመንግስት አካላት ተገቢውን ክትትልና ጥበቃ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

"በየአህጉረ ስብካታቸው የሚላኩትን ኤጵስ ቆጶሳት በታላቅ ፍቅርና አክብሮት እንድትቀበሉና ለመንፈሳዊ ሕይወታችሁ ማደግ እንድትተጉ" በማለትም ለኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ዝርዝሩን ለማግኘት : https://omnglobal.com/am/22394/

28/01/2023
25/01/2023
25/01/2023

“Yaawu Zaranyaadha naan jedhu, akkuma duratti jedhan sana. Maqaa tokko dhiisii lama, sadii, afurillee haa baasan. Ani kanaaf waanan sodaadhu hin qabu! Kun waan nama sodaachisus miti. Nuti ni sodaachisna malee hin sodaannu! Of ta’aa! Namni of hin taane biyyaafis, firaafis ollaafis hin ta’u! Nuti ijoolleen keenya afaansheetiin haa barattu, amantaan haa babal’atu jenne. Isaanimmoo lafaafi qabeenyaa dhabna jedhanii dhiphatu malee waan biraa miti!”

(Abbaa Saawiroos)

Kutannoo!

25/01/2023
29/12/2022
14/10/2022
🌀✅ የእጅ ጣታችን ርዝመት ስለ ማንነታችን ወይም ባህሪያችን ይገልፅ ይሆን? ከዚህ በታች የምንመለከታቸው ምስሎችም የቀለበት ጣታችንና ሌባ ጣታችን ያላቸውን ርዝመት በማነፃፀር ባህሪያቶቻችን ለ...
06/10/2022

🌀✅ የእጅ ጣታችን ርዝመት ስለ ማንነታችን ወይም ባህሪያችን ይገልፅ ይሆን?

ከዚህ በታች የምንመለከታቸው ምስሎችም የቀለበት ጣታችንና ሌባ ጣታችን ያላቸውን ርዝመት በማነፃፀር ባህሪያቶቻችን ለማወቅ ያስችላሉ ተብሏል።

ምስሎቹ በጣታችን ርዝመት መሰረት A, B እና C በሚል የተቀመጡ ሲሆን፥ እርስዎም የጣትዎን ርዝመት በመመልከት በየትኛው እንደሚመደብ ከለዩ በኋላ ከዚህ በታች የተቀመጡት መግለጫዎች ከተጨባጭ ማንነትዎ ጋር ይስማማሉ አልያም ይቃረናሉ የሚለውን እንዲመለከቱ ጋብዘናል።

1) "A"

የቀለበት ጣት ከሌባ ጣት መብለጡን የሚያሳይ ነው - ምስል “A”።
በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች የቆንጆ ተክለሰውነት ባለቤት መሆናቸው ይነገራል።

ሌሎች ሊያገኙት የሚጓጉለትን ነገር በቀላሉ ለማግኘት እንደሚችሉም ነው መረጃው የሚያመላክተው።

በተጨማሪም እጅግ በጣም ተናዳጅና ለውሳኔ የፈጠኑና አደጋን ለመቀበል የማይፈሩ ናቸው ተብሏል።

አብዛኞቹ ወታደሮች፣ ኢንጂነሮችና ቼዝ ተጫዋቾች ሲሆኑ የቃላት ድርደራ ጨዋታዎችን በመጫዎት የሚያህላቸው የለም።

የቀለበት ጣታቸው ከሌባ ጣታቸው የሚረዝም ሰዎች አጭር የቀለበት ጣት ካላቸው ሰዎች ይልቅ የተሻለ ገቢ እንደሚያገኙም ሳይንቲስቶች አረጋግጠዋል።

2) "B" በዚህ ምስል ላይ እንደምንመለከተው የቀለበት ጣት ከሌባ ጣት የሚያጥር ሲሆን፥ አጭር የቀለበት ጣት ያላቸው ሰዎች ከፍተኛ በራስ የመተማመን የተላበሱ መሆናቸው ይነገራል።

ራስ ወዳድነትና ትእቢት ቢጤ የሚያጠቃቸው እንደሆኑም መረጃው ይገልፃል።

ብቻቸውን መሆን የሚያስደስታቸው ሲሆን በእረፍት ስአታቸው መረበሽን አጥብቀው የሚጠሉ ናቸውም ተብሏል።

በፍቅር ግንኙነት ውስጥ ለመግባት ይፈራሉ የተባሉት ይህ አይነት የጣት አወቃቀር ያላቸው ሰዎች፥ በሌሎች ሰዎች እይታ ውስጥ መግባትን ግን የሚያደንቁና በጣም የሚፈልጉ ናቸው።

3) "C" የቀለበት ጣትና የሌባ ጣት እኩል መሆናቸውን የሚያሳይ ነው።

ሌባ ጣታቸውና የቀለበት ጣታቸው እኩል የሆኑ ሰዎች ሰላም ወዳድ እና ፀብና አለመረጋጋት ባለበት ቦታ ድርሽ ማለት የማያሹ ናቸው።

እነዚህ ሰዎች ለነገሮች ትኩረት የሚሰጡና የተቀናጁ ሲሆኑ፥ ከበርካታ ሰዎች ጋር በቀላሉ የመግባባት ብቃት አላቸው።

ለፍቅር ግንኙነትም ታማኝና ቅን ልቦና ያላቸው መሆኑ የሚነገር ሲሆን፥ አመለ ሸጋና ለፍቅር አጋራቸው እንክብካቤ የሚያበዙና የሚጠነቀቁ አይነት ሰዎች ናቸው።

እስኪ እርሶም ይሞክሩትና ማንነትዎን ይገልፃል አይገልፅም የሚለውን ያረጋግጡ።

ምርጥ መጣጥፎች
ሼርርርር

05/10/2022

የተከበሩ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመሩት ትምህርት ሚኒስቴር በሃገሪቱ መንግስት እውቅና በተቸረው የነቢዩ ሙሐመድ (ሰዓወ) የመውሊድ በዓል ተማሪዎችን ለፈተና መጥራት ፍፁም ተገቢ አይደለም።
ይህ ተደጋጋሚ "ስህተት" አስቸኳይ እርምት ሊደረግበት ይገባል።

27/06/2022
21/06/2022

በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ እና እጅግ በጣም ሩህሩህ በሆነው

ከጊዜያዊው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት አመራር በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

ከቅርብ አመታት ወዲህ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ብሄር፣ ማንነት እና ሃይማኖት ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች ሲሰነዘሩ ሙስሊሙ ማኀበረሰብ ሲያወግዝ፣ ለጉዳቱ ተጠቂዎች አቅም በፈቀደ ድጋፍ ሲያደርግ እና ዘላቂ ሰላም የሚያመጡ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ ይታወቃል ።

የአንድ ሃገር ዜጋ በሃገሩ በሰላም የመኖር ከምንም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው መሰረታዊ መብት ነው።
ባለፉት ጊዜያት በአማራ፣ ቤኔሻንጉል፣ በኦሮሚያ ክልል በወለጋ የተለያዩ አካባቢዎች እና በጋምቤላ ክልሎች ብሄር፣ማንነትን እና ሃይማኖትን መሰረት ባደረገ ዘግናኝ፣ አሰቃቂ ጥቃት እና ግድያ የበርካታ ንፁሐን ዜጎች ህይወት ማለፉን ከተለያዩ መረጃዎች ማረጋገጥ ችለናል። በተለይም በቅርቡ በመሰጊድ የተጠለሉ ምእመናንን ሳይቀር የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸው የድርጊቱን አጸያፊነት ያሳያል።

ይህን የሃይማታዊውንም ሆነ የዓለማዊ ህግ የጣሰ አጸያፊ የጥቃት እና የግድያ ወንጀልን ጊዜያዊ ጠቅላይ ምክር ቤቱ በጽኑ ያወግዛል።
በቀጣይም፡-
1. የፌዴራል መንግስት፣ የክልል መንግስታት እና የሚመለከታቸው አካላት ይህን አጸያፊ ድርጊት እና በወንጀል የፈጸሙ አካልን በአስቸኳይ ለህዝብ አሳውቀው እና ለፍርድ እንዲያቀርቡ
2. በጥቃት ከቤት ንብረታቸዉ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀደመ ህይታቸው እንዲመለሱ፣ ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኙ እና በዚህ ጥቃት እና ወላጅ አልባ የሆኑ ህፃናት ህብረተሰቡ ድጋፍ እንዲያደርግ
3. የወደሙ የግለሰብ፣ የህዝብ ንብረት እና የእምነት ቦታዎችን ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ እናሳስባለን።

በአጠቃላይ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ማንኛውም በንፁኋን ሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚቃጡ ጥቃቶች እያወገዘ የሃገሪቱ ህልውና መሰረት የሆኑትን የአብሮነት፣ መከባበርና እና መተዛዘን እሴቶች መመናመንና የስርአት አልበኝነትና ጭካኔ መበራከት ጉዳዩን የበለጠ አሳሳቢ ያደርገዋል።

በቀጣይም መሰል ጥቃቶች እና ወንጀሎች እንዲቆሙ እና ዜጎች በሰላም በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች እንዲንቀሳቀሱ የፊደራል መንግስትም ሆነ የከልል መንግስታት ብሎም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በጋራ በመተባበር ሌት ተቀን እንዲሰሩ እያሳሰብን የሃይማኖት ተቋማትን ጨምሮ ሌሎችም የሚመለከታቸው ወገኖች በዚህ ረገድ የበኩላቸውን ኋላፊነት በመወጣት መሰል ጥቃቶች እንዳይከሰቱ የመፍትሄ መንገዶች ላይ መስራት እንዳለባቸው ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በመጨረሻም ም/ቤታቸን ለሀገራችን ሁለታናዊ ሰላም መረጋገጥ ከሚመለታቸው አካል ጋር ጠንክሮ በመስራት ኃላፊነቱን ለመወጣት ዝግጁነቱን ያረጋግጣል።

አላህ ዓለማችን እና ሀገራችን ሰላም ያድርግልን!

ሰኔ 14/2014
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

21/05/2022
20/05/2022
19/05/2022

ለጠቅላላ እውቀት!

🐪 ግመል የበደለውን እንደማይረሳ ያውቃሉን?!!

🐘 ዝሆን ሀዘን ሲሰማው እንደሚያለቅስ ያውቃሉ?!!

🐊 አዞ ሲደሰት እንደሚያለቅስ ያውቃሉን?!!

🦁 አንበሳ የአውራ ዶሮ ጩኸትን እንደሚፈራ ያውቃሉ?!!

=> ፈረስ ጅራቱ ከተቆረጠ እንደሚሞት ያውቃሉ?!!

🦒ቀጭኔ በቀን ሶስት ጊዜ፤ በጥቅሉ ለ9 ደቂቃዎች ያህል ብቻ እንደምትተኛ ያውቃሉን ?!!

🐋 ዶልፊን 🦈 ሲተኛ አንድ አይኑን ብቻ እንደሚጨፍን ያውቃሉን?!!

🌑 ጂኒን የሚፈራው ቀበሮ ሳይሆን፤ ጂን ቀበሮን እንደሚፈራ ያውቃሉን?!!

🦅 ንስር አሞራ በህመም ምክንያት እራሱን በማጥፋት እንጂ በኖርማል
ሁኔታ እንደ ማይሞት ያውቃሉን?!!

🐜 ጉንዳን ስታስነጥስ እራሷን እንደምትስት ያውቃሉን?!!

በመጨረሻም ኀያሉ ፈጣሪያችን ጥራት ይገባው ማለት ይገባናል።

የትኛው አግራሞትን ፈጠረባችሁ ??

18/05/2022
07/05/2022

የሃሰት ዶክመንተሪው ከፋና ዩቲዩብ ቻናል መነሳት ጉዳቱን አያጠፋውም፤ ተቋሙ በህግ መጠየቅ ይኖርበታል:

05/05/2022

እየሱ'ስ ክርስቶ'ስ አምላክ #ላለመሆኑ 10 ወሳኝ ማስረጃዎ'ች‼
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
http://goo.gl/l9WyYf https://goo.gl/6DMB83

1- እየ'ሱስ ክር'ስቶስ አልነበረም፡፡ ‼

እንደሚታወቀው አምላክ ሁሉን አዋቂ ነው፡፡ ከዕውቀቱ የሚደበቅ ምንም ነገር የለም፡፡ እ'የሱስ ክርስ'ቶስ ግን እንደ መፅሀፍ "ቅዱ'ስ" ገለፃ ይህንን መስፈርት አያሟላም፡፡

" ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ #ልጅም [ኢየሱስ ክርስቶስም] ቢሆን ከአባት [ከእግዚአብሔር] በቀር ።"
(የማርቆስ ወንጌል 13:32)

2- እየሱስ ክርስቶስ አንዲትም ጊዜ ብሎ አያቅም‼

በብሉይ ኪዳን እግዚአብሄር እጅግ ብዙ ቦታዎች ላይ አምላክነቱን ሲያውጅና ሲገልፅ እንመለከታለን!
እየሱስ ክርስቶስ ግን በተቃራኒው ስለዚህ ጉዳይ ትንፍሽ አላለም፡፡
እስኪ ከብሉይ ኪዳን ለአብነት እንመልከት‼

" እግዚአብሔርም አለው። ፤ ብዛ፥ ተባዛም፤ "
(ዘፍጥረት 35:11)

" አለውም። የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤ ወደ ግብፅ መውረድ አትፍራ፥ በዚያ ትልቅ ሕዝብ አደርግሃለሁና።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 46:3)

"እግዚአብሔርም ሙሴን አለው። የእስራኤልን ልጆች ማንጐራጐር ሰማሁ። ወደ ማታ ሥጋን ትበላላችሁ፥ ማለዳም እንጀራን ትጠግባላችሁ፤ እኔም እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ በላቸው። "
(ኦሪት ዘጸአት 16:11,12)

" ከግብፅ ምድር ከባርነት ቤት ያወጣሁህ እግዚአብሔር ። "
(ኦሪት ዘጸአት 20:2)

3- እየሱስ በአዲስ ኪዳን የሰው ልጅ ተብሎ ተጠርቷል‼ እራሱ መፅሀፍ "ቅዱስ" እንደሚነግረን ደግሞ ይነግረናል‼

" ኢየሱስም። ለቀበሮዎች ጉድጓድ ለሰማይም ወፎች መሳፈሪያ አላቸው፥ ለሰው ልጅ ግን ራሱን የሚያስጠጋበት የለውም አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 8:20)

" ነገር ግን በምድር ላይ ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ለሰው ልጅ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ፥ በዚያን ጊዜ ሽባውን። ተነሣ፤ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 9:6)
http://goo.gl/l9WyYf https://goo.gl/6DMB83

" የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና።"
(የማቴዎስ ወንጌል 12:8)

" ለደቀ መዛሙርቱ። የሰው ልጅ በሰው እጅ ይሰጥ ዘንድ አለውና እናንተ ይህን ቃል በጆሮአችሁ አኑሩ አለ።"
(የሉቃስ ወንጌል 9:44)

ሌላ ቦታ ባይብልን ስናነብ ደግሞ የሰው ልጅ መታመን እንደሌለበት ይነግረናል፡፡

(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 146)
----------
1፤ ሃሌ ሉያ። ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን አመስግኚ።

2፤ በሕይወቴ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤ በምኖርበት ዘመን ሁሉ ለአምላኬ እዘምራለሁ።

3፤ ማዳን በማይችሉ በሰው ልጆችና በአለቆች አትታመኑ።

4- እየሱስ ክርስቶስ የነበረው ስልጣንና ሀይል የእርሱ አልነበረም፡፡‼

✔ " ኢየሱስ አብ ሁሉን በእጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥"
(የዮሐንስ ወንጌል 13:3)

✔ " እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 12:49)

✔" እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።"
(የዮሐንስ ወንጌል 5:30)

✔ " ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም፤"
(የዮሐንስ ወንጌል 7:16)

Like & Share ከተደረገ ይቀጥላል .......
Click and Like ➤➤ http://goo.gl/l9WyYf https://goo.gl/6DMB83 http://goo.gl/l9WyYf https://goo.gl/6DMB83

04/05/2022

የአማራ ክልል መጅሊስ ለህዝበ ሙስሊሙ ያስተላለፈው አደራ.. .
❝...ይህን በጎንደር ከተማ በሙስሊሞችና በእምነታችን ላይ የተቃጣዉን ጥቃት በአለም ላይ የምትገኙ ሙስሊሞች ድርጊቱን በማንኛዉም መንገድ እንድታወግዙትና የቀጣይ የመፍትሄ አካል እንድትሆኑ ጎንደር ላይ ሸሂድ በሆኑት ሙስሊሞች ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን..❞.
© የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ጠ/ም/ቤት ሚያዝያ 19 ካወጣው መግለጫ የተወሰደ

04/05/2022

በዒድ በዐል የአድማ ብተና የጭስ ቦንብ በማፈንዳት ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት ወንጀል የተጠረጠረው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ፍርድ ቤት ቀረበ።

በአዲስ አበባ በተከበረው በኢድ አልፈጥር በዓል ላይ የአድማ ብተና የጭስ ቦንብ በማፈንዳት ወንጀል የተጠረጠረው የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ውሎ ፍርድ ቤት መቅረቡ ተሰምቷል።

የፌደራል ፖሊስ አድማ ብተና ዘርፍ አባል የሆነው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በቁጥጥር ስር ውሎ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በዛሬው እለት ረፋድ ላይ መቅረቡ ነው የተነገረው።

በችሎቱ መርማሪ ፖሊስ ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በኢድ አልፊጥር በዓል ዕለት በተመደበበት ወንጀል የመከላከል ምደባ ላይ እያለ የታጠቀውን አድማ በታኝ የጭስ ቦንብ በአግባቡ መታጠቅ ሲገባው በአግባቡ ባለመታጠቅ የጭስ ቦንቡ እንዲፈነዳና ሁከትና ብጥብጥ እንዲፈጠር አድርጓል ያለው ሲሆን፣ በዚህ በተፈጠረ ሁከትና ብጥብጥ የመንግስትና የግለሰብ ንብረት ጉዳት መድረሱንም አብራርቷል።

በተጠረጠረበት ሁከትና ብጥብጥ ማስነሳት ወንጀል ለተጨማሪ ማስረጃ አሰባስቦ ለመቅረብ 14 ቀን እንዲሰጠው መርማሪው ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

ተጠርጣሪው ኮንስታብል አንቡላ ኡቴ በበኩሉ በዕለቱ አስቀድሞ በተመደበበት ቦታ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ እንደነበር እና በሰዓቱ በቦታው ላይ የነበሩ ሰዎች ቁጥር መጨመርና መጨናነቁን ተከትሎ ከታጠቀው ሶስት አድማ በታኝ የጭስ ቦንብ ውስጥ አንደኛው በማያውቀው ሁኔታ መሬት ላይ ወድቆበት በድንገት መፈንዳቱን ገልጿል።

ሆኖም ምንም አይነት ተንኮልም ሆነ ክፋት በውስጤ አልነበረም ወድቆ ሲፈነዳ እኔ ራሴ ደንግጬ ነበር ሲል እያለቀሰ ሁኔታውን ለችሎቱ አስረድቷል።

በተጨማሪም ተጠርጣሪው ወላጆቹን በሞት ማጣቱን ገልጾ እህትና ወንድሙን በሱ እርዳታ እያስተማራቸው እንደሆነ እና ከሌሊት 7 ሰዐት ጀምሮ ለጥበቃ ስራ ከመሰማራቴ ውጪ ሌላ ክፋት በውስጤ የለም ሲል ለችሎቱ አብራርቷል።

ጉዳዩን የተከታለው ፍርድ ቤቱ ለተጨማሪ ምርመራ ለፖሊስ 14 ቀን በመፍቀድ ለግንቦት 10 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል መባሉን የችሎት ጉዳዮች ጋዜጠኛዋ ታሪክ አዱኛ ዘግባለች።

04/05/2022

ከለውጥ ወዲህ ብቻ በነበሩት ባለፉት 4 ዓመታት በአማራ ክልል ስልጣን ላይ በነበሩ አምስት የክልሉ ፕሬዝዳንቶች ዘመን በክልሉ ሙስሊሞች ላይ ከሞጣ እስከ እስቴ፥ከጃራ ገዱ እስከ ቢቸና፥ ከጭልጋ እስከ ጎንደር በተደጋጋሚ ጊዜ ሃይማኖትን መሠረት ባደረገ መልኩ ከሠላሣ በላይ መስጊዶች ሲቃጠሉና ሲጠቁ፥የሙስሊሞች ሱቆችና ቤቶች ተለይተው ሲዘረፉና በርካቶች በተገደሉበት በንጹሃን ሙስሊሞች ላይ የሽብር ጥቃቶች ሲፈጸሙ «ለእውነት፥ ለፍትህ፥ ለዲሞክራሲና ለሕግ የበላይነት ቆመናል» የሚሉት የደሴቷ ናፋቂ ሚዲያዎች ፥አክቲቪስቶች፥ጋዜጠኞች፥ የክልሉ ባለስልጣናት፥ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽንና ሌሎች አካላት ጭምር አንዳቸውም ቢሆኑ የለበጣ «ድርጊቱ አስነዋሪ ነው።»፥ «እኛም አውግዘነዋል።»፥«የድርጊቱ ፈጻሚዎች ሕዝቡን አይወክሉም።» ፣«ከተማችን ወደ ቀድሞ ሰላሟ ተመልሳለች።» ወዘተ በማለት ለማድበስበስ ይሠራሉ።ዋናው ጥያቄና ጭብጥ የድርጊቱ ፈጻሚዎች ማንን ይወክላሉ! የሚለው ሳይሆን ለፈጸሙት የሽብር ወንጀል ተጠያቂ ተደረጉ ወይ የሚለው ነበር።

ሆኖም ከጅምሩ ዓላማቸው የችግሩን መጠን ማቃለል ፣ለወንጀለኞቹ ሽፋንና ከለላ መስጠት፣ ለእውነትና ፍትህ ከመወገን የራስን የጠለሸ ስም ማደስ በመሆኑ የተፈጸሙት ወንጀሎች በተደጋጋሚ ጊዜ ሆነ ተብለው ተድበስብሰው ቀሩ።

ከዚያ ሁሉ ባለሚዲያ፣አክቲቪስት፣የመብት ተሟጋች፣ ጋዜጠኛ፣ታዋቂ ሰዎችና ሰባኪያን መካከል «የሽብር ጥቃቶቹ ጉዳዩ ሳይድበሰበስ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ወንጀል ፈጻሚዎቹ ላይ አስተማሪ የሆነ ፍርድ ሊያገኙ ይገባል» ብሎ ለተግባራዊነቱ እስከመጨረሻው የሞገተና ለእውነት የቆመ አንድም አካል አላየንም። እንዲያውም ከፊሎቹ የሐሰት ዉንጀላዎቹን በመደገፍ ላይ ተጠምደው ተገኙ። በአንዱም የሽብር ጥቃት ላይ እንኳን የተሳተፉ ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር ዉለው ፍርድ አግኝተው አለማወቃቸው በራሱ ችግሩ የተቀናጀና መዋቅራዊ መሆኑን ያስገነዝበናል። ለዚህም ነው በአሁኑ የጎንደር የሽብር ጥቃት ፈጻሚዎችም በተለመደው መንገድ «በቁጥጥር ስር ዋሉ» የሚለው ዘገባም የሽብር ፈጻሚዎቹ ጉዳይም እንደከዚህ ቀደሞቹ በዚያው በአማራ ክልል የሚታይ ከሆነ ዜናው ማስተኛ ኪኒን ከመሆን አይዘልም።

ለነዚህ ጥቃቶቹ ሁሉ ሽፋን ሲሰጡ፥ ጉዳዩቹን ለማቃለል ሲተጉ፥ ችግሮቹን ዉጫዊና የጠላት ሴራ አድርገው በማቅረብ ራሳቸውን ንጹህ ሲያደርጉ ለተበዳዮቹ ድምጽ በመሆኔ «አጋለጠን»፥«ልናፍነው የፈለግነውን ድምጽ እንዲስተጋባ አድረገ» በሚል ቁጭት የገዛ ወገኖቻቸው እስኪታዘቧቸው ድረስ እኔኑና መስሊሞችን መልሰው ለመወንጀል ተፍጨረጨሩ። እንደለመዱት የኔን ስምና ገጽታ ለማጠልሸት የፈጠራ ዜናዎችን በየጓዳዎቻቸው እየፈበረኩ በሚዲያዎቻቸው ተቀባበሉ።አሰራጩ።

በተቆጣጠሩዋቸው ሚዲያዎቻቸው በኩል በለመዱት የሀሰት ክስ ጋጋታ ላይ ተንተርሰው ጠልፎ የመጣል ዘመቻቸውን ጀመሩ።የማታውም ዶኪዩመንተሪ ተበዳይን የመክሰስ፣የጎንደሩን ጥቃት የማቃለልና የችግሩን ሥረ መሠረትን ከዋናው ሥፍራ ለማራቅ ዓላማን ያነገበና ከዚሁ የሚዲያ ጦርነት ጎራ የሚመደብ ነው።

ሚዲያውን የተቆጣጠሩት አካላት በዘገባዎቻቸውም ሆነ ዘጋቢ ፊልሞቻቸው፣ ስለጉዳዩ መግለጫ የሚሰጠው የመንግስት አካልም ለጎንደሩና መሰል የሙስሊሞች ጥቃቶችን ስላነሳሱት የሽብር ቅስቀሳዎች ከስር ባለው የቴሌግራሜ ቻናል( https://t.me/ahmedin99/4273 ) ላይ ስለተያያዙት ቪዲዮዎች እያወቁ እንዳላዩ ማለፍን መርጠዋል።ተሳክቶላቸው ጥቂት ወደነዚህ የሽብር ቅስቀሳዎች ቀረብ የሚል የጥቂት ሰከንዶች የኔን ቪዲዮ ወይም ድምጽን ቢያገኙ የዘወትር ጸሎት ያክል ደጋግመው ለሕዝባቸው ባሰሙም ነበር።

የቴሌግራም ቻናሌ ላይ የተያያዘውን ቪዲዮ ሊንኩን በመጫን ይመልከቱ። 👇

https://t.me/ahmedin99/4273

02/05/2022

Miciyyoon tuni Dambal buufata Pooliisi jirti maatii biraan nuugahaa bilbila kanaan dhaqanii hqqbarbaaddatan
Saajin ALAMAAYYEHUtti bilbiladhlaa dhaqaa fudhaa maalo daa`imaa duudaa uffffeee Yaa Allaah

በኢዱ ግርግር የጠፋች ህፃን ቤተሰቧን አፋልጉን የጠፋች ህፃን ናት ደምበል ፖሊስ ጣቢያ
ትገኛለች ለቤተሰቧ ይድረስ ሼር ሼር
ዋና ሳጅን አለማየው ጋር ደውለው ይወሰዷት 0915534862

02/05/2022
02/05/2022
27/04/2022

Address

Addis Ababa
1000

Telephone

+251917298115

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sahibu Page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sahibu Page:

Videos

Share

Category