Amhara Tourism Attractions

Amhara Tourism Attractions Tourism sites are disclosed here

አድሷ አምባሰደር መልካም የስራ ዘመን!
31/01/2025

አድሷ አምባሰደር

መልካም የስራ ዘመን!

የአገው ፈረሰኞች ደማቅ አከባበር እየተከናወነ ነው።
31/01/2025

የአገው ፈረሰኞች ደማቅ አከባበር እየተከናወነ ነው።

በ85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማህበር በዓል በተካሄደው የወይዘሪት አገው ምድር የቁንጅና ውድድር  ቤተልሔም አዳሙ አሸናፊ ሆናለች።
30/01/2025

በ85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማህበር በዓል በተካሄደው የወይዘሪት አገው ምድር የቁንጅና ውድድር ቤተልሔም አዳሙ አሸናፊ ሆናለች።

እንጅባራ አሸብርቃለች ! የአርበኝነት ተምሳሌት ያለውን የአገው ፈረሰኞች በዓል በልዩ ድባብ ለማክበር ዝግጅት አጠናቀዋል። #አድናስ
30/01/2025

እንጅባራ አሸብርቃለች ! የአርበኝነት ተምሳሌት ያለውን የአገው ፈረሰኞች በዓል በልዩ ድባብ ለማክበር ዝግጅት አጠናቀዋል።
#አድናስ

"ደረስጌ ማርያም ቴዎድሮስ የነገሠባት፣ ደጋጎች የሚኖሩባት" ስለዓለም ምህረት እና ሰላም ይለመንበታል። ዓለምን  የናቁ ደግ እና ሩህሩህ አባቶች የምድሩን ሳይኾን ሰማያዊ ዋጋን አስበው በምሥጋ...
29/01/2025

"ደረስጌ ማርያም ቴዎድሮስ የነገሠባት፣ ደጋጎች የሚኖሩባት"

ስለዓለም ምህረት እና ሰላም ይለመንበታል። ዓለምን የናቁ ደግ እና ሩህሩህ አባቶች የምድሩን ሳይኾን ሰማያዊ ዋጋን አስበው በምሥጋና ሲደክሙ ያድሩበታል ደረስጌ ማርያም።

ይህች ታላቅ ሥፍራ ሊቃውንቱ ከዓመት እስከ ዓመት ያመሰግኑባታል። ልብን በሚመስጥ ዜማ ስብሐተ እግዚአብሔር ያቀርቡባታል። በአስተርዮ ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል ደግሞ በብዙ ሕዝብ ትከበባለች። በሊቃውንቱ ትታጀባለች።

ደረስጌ ማርያም በአስተርዮ ማርያም ክብረ በዓል ከአራቱም አቅጣጫ በሚሠባሠቡ አማኞች ትደምቃለች። ይህ ቀን ለደረስጌ ማርያም ልዩ ነው።

የጃናሞራ ወረዳ ባሕልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ቄስ መሳፍንት አማረ እንደነገሩን ደረስጌ ማርያም በሰሜን ጎንደር ዞን ጃናሞራ ወረዳ ከመካነ ብርሃን ከተማ በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።

ደረስጌ ማርያም በጎንደር ዘመን በአድያም ሰገድ ኢያሱ እንደተመሠረተችም ነግረውናል። በ1818 ዓ.ም ደግሞ የስሜኑ ገዥ ራሥ ውቤ ኃይለማርያም እንደገና አንጸዋታል ይላሉ። አሁን ያለው ኪነ ሕንፃ እና ቅርስ በራስ ውቤ አማካኝነት የተገነባ ነው።

ደረስጌ ማርያም ዘመነ መሳፍንትን የቋጩት፣ ለአንዲት ኢትዮጵያ አንድነት የታተሩት፣ አጼ ቴዎድሮስ በከፍታ ላይ ቆመው የተቀቡባት ታሪካዊት ሥፋራ ናት። እርሳቸው የተቀቡበት ሰገነትም በቅጥር ግቢው ውስጥ በክብር ቆሞ እንደሚገኝ ነግረውናል።

ደረስጌ ማርያም የአጼ ቴዎድሮስ ባለቤት እና የልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ እናት የእቴጌ ጥሩወርቅ የትውልድ ቦታም ናት ይላሉ። ይህች ሥፋራ የዘመነ መሳፍንት ፍጻሜ የተበሰረባት ናትና በልዩ ሁኔታ ትታያለች።

በዚህም ደረስጌ ለዘመናዊቷ ኢትዮጵያ መነሻ፣ አጼ ቴዎድሮስ መናገሻ ናትና በታሪክ ስትታወስ ትኖራለች ነው የሚሉት። በወርቅ ቅብ ጉልላት አጊጣ የተሠራችው ደረስጌ ማርያም ከደጃች ውቤ እና ከዳግማዊ ቴዎድሮስ ጋር የሚገናኙ በርካታ ቅርሶችን የያዘች ቤተ ክርስቲያንም ናት፡፡

ደረስጌ ማርያም በወርቅ እና በብር የተንቆጠቆጡ ከበሮዎች፣ ከጎሽ ቀንድ የተሠሩ ዋንጫዎች፣ የነገሥታት ዘውዶች፣ የንግሥና አክሊሎች እና ሌሎችም ቅርሶች በውስጧ አቅፋ ይዛለች። የተለያዩ የወርቅ እና ብር መስቀሎች፣ የብራና መጻሕፍት እና ሌሎችም ቅርሶች በቤተ ክርስቲያኗ ይገኛሉ፡፡

ደረስጌ ጽርሐ ጽዮን ማርያም አሰገምጋሚ ድምጽ ያለው የደወል ቅርስም ባለቤት ናት። ደወሉ ያለ ቁርጥ ነገር አይደወልም ይባላል። ይህ ደወል የሚደወለው አንድም በአካባቢው ላይ አስጊ ነገር በተከሰተ ጊዜ ተጠራርቶ ለመከላከል፣ ሁለትም ፍጹም የኾነ ደስታን የያዘ ክብረ በዓል የደረሰ ዕለት ነው ይህ ደወል የሚደወለው።

ይህ አስገምጋሚ ድምጽ ያለው ደወል በዓመት ውስጥ ሁለቴ በሚከበሩ የደረስጌ ጽርሐ ጽዮን ማርያም የደስታ ቀናት ይደወላል። በሕኅር 21 እና በጥር 21 ቀናት።

በደረስጌ ጽርሐ ጽዮን ማርያም ዓመታዊ የንግሥ በዓል ላይ የሀገሬው ሰው በአስገምጋሚው ደወል ድምፅ ተጠራርቶ በእልልታ እና በሆታ ይጓዛል። የንግሥናም የቅድስናም ቦታ በኾነችው ድንቋ ደረስጌ ማርያም ላይ ዕድል ቀንቶት የተገኘ ሁሉ የሚያስደንቀውን ሥርዓት ይመለከታሉ።

ቅርሶቿን ለጎብኝዎች ምቹ እንዲኾኑ ሙዚየም ተገንብቶ መጠናቀቁንም ነግረውናል። አሁን ላይ የቅርስ ማስቀመጫው እየተሠራ ነው ብለውናል።

ዛሬ ደረስጌ ከሁሉ በላይ አምራ እና ተውባ በአማኞቿ አጊጣ እየከበረችም ነው። የቻሉት በአጸዷ ሥር ተገኝተው ምስጋና እያቀቡባት ነው። ያልቻሉት ደግሞ በዓይነ ህሊናቸው ያስቧታል።

Visit Amhara Amhara Media Corporation

የድንቅ ምድር የጥር ወር ቀጣይ ሀይማኖታዊና ባህላዊ ክብረ በዓላት🇪🇹ጥር 21 - አስተርዮኦ ማርያም (በመርጡለ ማርያም፣ ደረስጌ፣ ግሸን ደብረ ከርቤ፣ ሎዛ ማርያም እና በክልሉ ሁሉም አካባቢዎ...
28/01/2025

የድንቅ ምድር የጥር ወር ቀጣይ ሀይማኖታዊና ባህላዊ ክብረ በዓላት
🇪🇹
ጥር 21 - አስተርዮኦ ማርያም (በመርጡለ ማርያም፣ ደረስጌ፣ ግሸን ደብረ ከርቤ፣ ሎዛ ማርያም እና በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች)

ጥር 23 – 85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማህበር በዓል (በእንጅባራ)

ጥር 25 - የቅዱስ መርቆሪዮስ በዓል (በደብረ ታቦር እና እስቴ)

ይምጡ! ድንቅ በዓላትን ከእኛ ጋር ያክብሩ!

Visit Amhara

በአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ለክብር እንግዶች  የሚቀረቡ ባህላዊ ምግቦች በከፊል፤📸
27/01/2025

በአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ለክብር እንግዶች የሚቀረቡ ባህላዊ ምግቦች በከፊል፤

📸

የሰባር ጊዮርጊሥ ክብረ በዓል ባሕር ዳር እየተከበረ ነው****** የሰባር አጽሙ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊሥ ካቴድራል  በድምቀት እየተከበረ ነው።የባ...
26/01/2025

የሰባር ጊዮርጊሥ ክብረ በዓል ባሕር ዳር እየተከበረ ነው
******

የሰባር አጽሙ ቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊሥ ካቴድራል በድምቀት እየተከበረ ነው።

የባሕር ዳር እና አካባቢው ምዕመናን በፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊሥ ካቴድራል ዙሪያ ታድመዋል።

የተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎችን ሲፈጽሙ ያደሩት ሊቃውንተ-ቤተክርስትያን እና አበው ካህናት ታቦተ ሕጉን ከቤተ ክርስቲያን በማውጣት ላይ ይገኛሉ።
communication

85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማህበር በዓል ደረሰ🐎🐎🐎    🏇🏇🏇ያ ሰው ማነው ባለፈረሱ፣ከፍብሎሚታይ ግርማ ሞገሱ፣በጃኖ ደምቆ ከእግር ከራሱ፣አትጠራጠር አገው ነው እርሱ።በአንድ በኩል አራሽ በሌላ...
24/01/2025

85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማህበር በዓል ደረሰ
🐎🐎🐎 🏇🏇🏇

ያ ሰው ማነው ባለፈረሱ፣
ከፍብሎሚታይ ግርማ ሞገሱ፣
በጃኖ ደምቆ ከእግር ከራሱ፣
አትጠራጠር አገው ነው እርሱ።

በአንድ በኩል አራሽ በሌላ ዘማች
የሆነው "የፈንዞ" ፣ "የጥርኝ"፣ "የዳማ"፣ "የሻንቆ"፣ "የቡላ" ...ጌታ በማለት ፈረሱን ከራሱ በላይ የሚያሞጋግሰው የአገው ማህበረሰብ እና የፈረስ ቁርኝት ልዩ ነው።

ፈረስ ለሰርግ
ፈረስ ለእርሻ
ፈረስ ለጭነት
ፈረስ ለለቅሶ
ፈረስ ህክምና (ባህላዊ አምቡላንስ)
ፈረስ ለጦርነት
ፈረስ አገው ምድር ላይ ለሁሉም ነገር ማጣፈጫ ቅመም ነው።

በወርሃ ጥር 1932 ዓ.ም ሃሳቡ ተጠንስሶ በ1933 ዓ.ም የተቋቋመው የአገው ፈረሰኞች ማህበር ዛሬ 85 ዓመታትን አስቆጥሯል።

Visit Amhara Visit Amhara

አስተርዮን - በግሸን ደብረ ከርቤ !------------ከደሴ ከተማ በስተ ሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ በ82 ኪ•ሜ ርቀት ላይ ከአምባሰል በማራኪ ከፍተኛ ተራሮች ላይ  የምትገኘዋ  ግሸን ደብረ ከር...
24/01/2025

አስተርዮን - በግሸን ደብረ ከርቤ !
------------
ከደሴ ከተማ በስተ ሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ በ82 ኪ•ሜ ርቀት ላይ ከአምባሰል በማራኪ ከፍተኛ ተራሮች ላይ የምትገኘዋ ግሸን ደብረ ከርቤ የተራራው አናት/አምባ

በመስቀለኛ ቅርጽ ተራራ አናት ላይ የምትገኘዋ እየሱስ ክርስቶስ የተሠቀለበት መስቀል የሚገኘባት ታሪካዊቷና ቅድስቷ ግሸን ደብረ ከርቤ እነሆ ጥር 21 ላይ ትደምቃለች።

ግሸን ደብረ ከርቤ ማሪያም ገዳም በአመት ሁለት ጊዜ መስከረም 21 እና ጥር 21 በሚከበሩት በዓላቶቿ በርካታ ቁጥር ያለው ይገኛል። እርስዎም በዕለቱ ይገኙ ዘንድ ተጋብዘዋል።

እግረመንገድዎን ሀይቅ እሰጢፋኖስ ገዳምን ይጎበኛሉ።


#ግሸን
#ኢትዮጵያ
#ተዋህዶ
#ወሎ

ጥር 23 የሚከበረው የአገው ምድር ፈረሠኞች አመታዊ ክብረ በዓል እየደረሠ ነው።Visit Amhara
22/01/2025

ጥር 23 የሚከበረው የአገው ምድር ፈረሠኞች አመታዊ ክብረ በዓል እየደረሠ ነው።
Visit Amhara

የጊዮን በዓል የጊዮን ወንዝ በታላቁ ቅዱስ መፅሐፍ 'መፅሐፍ ቅዱስ' አለምን ከሚከቡ አራቱ አፍላጋት መካከል አንዱ እንደሆነ ተጠቅሷል። ከዚህ ወንዝ መነሻ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች...
21/01/2025

የጊዮን በዓል
የጊዮን ወንዝ በታላቁ ቅዱስ መፅሐፍ 'መፅሐፍ ቅዱስ' አለምን ከሚከቡ አራቱ አፍላጋት መካከል አንዱ እንደሆነ ተጠቅሷል።
ከዚህ ወንዝ መነሻ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጣቸው የፃድቁ አቡነ ዘርዓ ብሩክ ፀበል በመሆኑ በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ወረዳ ግሽ አባይ ከተማ ላይ ጥር 13 በታላቅ ድምቀት የጊዮን በዓል ተከብሮ ይውላል።

እንኳን አደረሳችሁ!
Visit Amhara

20/01/2025

ዛሬ የቃና ዘገሊላ በዓል በደማቅ ሁኔታ የሚከበርባቸው ቦታዎች ላይ ያሏችሁን ፎቶዎች በውስጥ መስመር ብትልኩልን በፔጃችን ለመልቀቅ ዝግጁ ነን። እናመሰግናለን

በተከዜ ወንዝ ዳርቻ የጥምቀት ስነስርዓት። #ወልቃይት አማራ
20/01/2025

በተከዜ ወንዝ ዳርቻ የጥምቀት ስነስርዓት።
#ወልቃይት አማራ

Address

Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Tourism Attractions posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category