የጌዴኦ ጥምር እርሻ

የጌዴኦ ጥምር እርሻ The farming style of Gedeo nation w/c founded in southern Ethiopia specially in Gedeo Zone-Dilla

የምጽፉ እጆች ይበረታታሉ!!ከጊዜ ወደ ጊዜ የጌዴኦ ህዝብ ምሁራን ተወላጆች በብሔሩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ ይዘት ያላቸውን መጽሐፍቶች በመጻፍ አሻራቸውን እያስቀመጡ ይገኛ...
24/01/2025

የምጽፉ እጆች ይበረታታሉ!!
ከጊዜ ወደ ጊዜ የጌዴኦ ህዝብ ምሁራን ተወላጆች በብሔሩ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ የተለያዩ ይዘት ያላቸውን መጽሐፍቶች በመጻፍ አሻራቸውን እያስቀመጡ ይገኛሉ።
''ዳማንቆ'' የተሰኘው በጸሐፊው አገላለጽ እንንቃ የሚል ዕሳቤ ያለው በርካታ የብሔሩን ታሪካዊ ስነምህዳራዊ እንቅስቃሴዎችን የምያስቃኝ መጽሐፍ በወጣት ጸሐፊ አቶ ወንድማገኝ አሰፋ ተጽፎ እሁድ በ18/5/2017 ዓ.ም በጌዴኦ ባህል አዳራሽ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ምሁራንና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በይፋ ይመረቃል።

23/12/2024
Gede'o cultural landscape  and sacride  forest : A Biodiversity Hotspot   !
09/11/2024

Gede'o cultural landscape and sacride forest : A Biodiversity Hotspot !

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Eliyasi Tadese Gobena, Etaferaw Bekele, Abrham Asefa Duka...
30/10/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Eliyasi Tadese Gobena, Etaferaw Bekele, Abrham Asefa Dukale, Hawa Teha, ከመከም ውሎ የው, Kibru KB, Abit Man Bayu, Amare Berehe Nega, Fiqe Godana, Lidetu Abera, Esmael Tezera, Getnet Werqu, Sami Menigesha Gedo, Ermias Kidane, Melese Tsega, Ephirem Haile Jisso, Mule Tade, Emebet Gadisa

የ"ባቦ" ሥርዓትና የቡና ትስስር ኢትዮጵያ እምቅ በሆነ በተፈጥሮ ሃብት የታደለች ሀገር ናት፤ ነገር ግን በተለያዩ ሰዉ ሰራሽና በተፈጥሮ ክስተቶች ሳቢያ ሀገሪቱ ያላት የደንና የተፈጥሮ ሀብቶች...
23/08/2024

የ"ባቦ" ሥርዓትና የቡና ትስስር

ኢትዮጵያ እምቅ በሆነ በተፈጥሮ ሃብት የታደለች ሀገር ናት፤ ነገር ግን በተለያዩ ሰዉ ሰራሽና በተፈጥሮ ክስተቶች ሳቢያ ሀገሪቱ ያላት የደንና የተፈጥሮ ሀብቶች ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡

እያደገ ከመጣዉ ከህዝብ ብዛት ጋር ተያይዞ ለምግብ አቅርቦት ሲባል በግብርና ዘርፍ ከፍተኛ የሆነ የአርሶ አደሩና ሰፋፊ የእርሻ መሬት ለማገዶና ለግንባታ ሥራ የሚያገለግል የእንጨት ፍላጎት መጨመር ለሰፈራና ለከተሞች መስፋፋት ሲባል የደን ምንጣሮና ቃጠሎ ዘርፈ ብዙ ለሆነው ለደን ሀብታችን መመናና መጥፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

እንደ አካባቢያው ስነምህዳር ይለያይ እንጂ በተለይ ደኖች ለሰው ልጆች በርካታ የሆኑና የሚጠቅሙ ነገሮችን አስተዋጽኦ ከማድረጉም የበለጠ የገቢ ምንጭ ጭምር ይሆናሉ፡፡

በዚህም የተነሳ በጌዴኦ ማህበረሰብ ዘንድ ደን ማለት “ ባቦ” ተብሎ የሚጠራ ሲሆን ይህ የባቦ ሥርዓት ባህሉን ከማስተዋወቅ ጎን ለጎን የግብርና ምርቶችን ለማልማት እንዲሁም ጠንካራ ኢኮኖሚ ለመገንባት የደን ወይም የባቦ አስተዋጽኦ ጎልቶ ይገኛል፡፡

ይህንን ጥቅም ምክንያት በማድረግ የሰው ልጅ ለራሱ የሚበጁትን እፅዋቶች ሲተክል ተፈጥሮ አብቅላው ደግሞ ለሰው ልጅ በሰጠችው ጥበብ ለመድኃኒትነት ለምግብነትና አንዱ ለአንድ ምግብ፣ አንዱ ለአንዱ ጥላና ከለላ ሆኖ እንዲኖር አስማምታዋለች፡፡

የምድር ተፈጥሯዊ የማስማማትና የማዋሃድ ጥበብ ላይ የሰው ልጅ ዕዉቀቱን አክሎበት የዕፅዋቱን ደህንነት የመሬቱን ደህንነት እየጠበቀ ለራሱና ለእንስሳቱ ብሎም ለአራዊቱ በሚስማማ መልኩ እየተጠቀመበት ይገኛል፡፡

የዚህ ተፈጥሯዊ ዕዉቀት ባለቤት ከሆኑ ሕዝቦች መካከል ጌዴኦች በዋናነት ተጠቃሾች ናቸው፡፡

ጌዴኦዎች ባረፉበት ወይም በሚገኙበት ቦታ ላይ 3 ነገሮች አይጠፉም ትላልቅ ዛፎች፣ ቡናና እንሰት በዋነኝነት ከጌዴኦ ህዝብ ጋር ያላቸው ቁርኝት ጥብቅ ከመሆን ባለፈ ይህንኑ ማህበረሰብ ተፈጥሮን በመንከባከብ አንዱ ከአንዱ ጋር ተስማምቶና አስማምቶ በማኖርም እንዲታወቅና መለያው እንዲሆነው አስችሎታል፡፡

ጌዴኦች ለእፅዋት ለደንና ለዛፎች ያላቸው ትኩረት ከፍተኛ በመሆኑ ከሚመሩበት ባህላዊ አስተዳደር ጎን ለጎን ለደን አያያዝና ጥበቃ የሚረዳ የባቦ ሥርዓት ዘርግተው ሲጠቀሙበትና አካባቢያቸውን ሲያለሙበት በርካታ መቶ አመታትን አስቆጥረዋል፡፡

የጌዴኦ ማህበረሰብ የደን ልማት በማጠናከር ካለዉ ቁርጠኝነት ተነስቶ ለምርትና ምርታማነትና ለኦርጋኒክና በተፈጥሮ ልዩ ጣዕም ያለዉን እንደ ይርጋጨፌ ያለዉን ቡና ለአለም ገበያ በማቅረብ ለሀገሪቱ ከፍተኛ የሆነ ገቢ ለማስገኘት አስተዋጽኦ ከፍ ያለ በመሆኑ በአካባቢ የሚገኘዉን ከመተዳደሪያው ባሌ ሥርዐትየ‹‹ባቦ››ን ጨልፎ በመተግበር ለደን ሃብት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠትና በመንከባከብ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን አስገኝቷል፡፡

‹‹ባቦ›› ማለት በጌዴኦ ማህበረሰብ አንዱን በቆረጡበት ቦታ ሁለትና ከዚያ በላይ ዛፎችን መልሶ በመትከልና በስርዓት በመንከባከብ ለምግብነትና ለገበያ የሚያመርታቸውን ቋሚም ሆነ ጊዜያዊ ሰብሎችን ደህንነት የሚጠብቅና ሲያልፍም ለመድኃኒትነት የሚዉሉ ዕፅዋቶች ችግኝ የሚተክልበት ሥርዓት ነው፡፡

በጌዴኦ ማህበረሰቡ ዘንድ ይህን የ‹‹ባቦ›› ባህልን አለመጠበቅ ሥርዓቱን አለመፈፀም ወይም ከተወቃሸነትም ባለፈ በወደፊት የልጆች የትዳር ሕይወትም ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩ አይቀርም ፡፡

በባህሉ ወግና ሥርዓቱ አባት ወንድ ልጁን ለመዳር ወደ ሴቲቱ ቤት ሽምግልና ቢልክ ከሴቷ ቤተሰብ የሚቀርበው ጥያቄ “ምን ያህል ኃብት አለው?››ሳይሆን “ምን ያህል ዛፎች አሉት?›› የሚል ጥያቄ ያነሳል፡

የደንና የአከባቢ ጥበቃ ጠበብቶቹ የጌዴኦ ብሔርጌዴኦ ደቡብ ኢትዮጵያ - ካዮ ፕሮሞሽን ዲላ የጌዴኦ ህዝብ ከቀደምት አባቶች ስወርድ ሲዋረድ የመጣ ተፈጥሮን የመጠበቅ ፤የመንከባከብ እና ከተፈጥሮ...
22/07/2024

የደንና የአከባቢ ጥበቃ ጠበብቶቹ የጌዴኦ ብሔር

ጌዴኦ ደቡብ ኢትዮጵያ - ካዮ ፕሮሞሽን ዲላ

የጌዴኦ ህዝብ ከቀደምት አባቶች ስወርድ ሲዋረድ የመጣ ተፈጥሮን የመጠበቅ ፤የመንከባከብ እና ከተፈጥሮ ጋር ተስማምቶ የመኖር ጥበብ ባለቤቶች ናቸው።

ዛፍ ህይወት መሆኑን ቀድሞ የተረዳው ማህበረሰቡ ጥብቅ ደኖችን ከሰውና ከተፈጥሮ ንክኪ ጠብቆና እንደ ልጅ ተንከባክቦ ከትውልድ ትውልድ የሚያነጋግር አኩሪ ባህል ያለው ድንቅ ህዝብ ነው።

በአጠቃላይ በጌዴኦ ደንና ተፈጥሮን ተንከባክቦ በመያዝና በመጠበቅ ለትውልድ የማቆየት ከህዝቡ አኗኗር ዘይቤ ጋር የተቆራኘ ባህል ነው።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ።

29/12/2023

Ashshama Duuchchiingi

የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር ሕጋዊ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ)፡፡ ዛሬ ህዳር 17/2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ ተረክባለች። ...
28/11/2023

የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር ሕጋዊ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ)፡፡ ዛሬ ህዳር 17/2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ ተረክባለች።
* ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ!
* ታታሪው የጌዴኦ ህዝብ ደስ ይበላችሁ

ከ    አንደበት ስለ ጌዴኦ ባቦ ወይም ስለ መልክዓ ምድሩ    vs     VS  'o               ✅ባቦ የሚባለው የጌዴኦ የግብርና ሥርዓት በዩኔስኮ (UNESCO) በመመዝገቡ እንኳን...
01/10/2023

ከ አንደበት ስለ ጌዴኦ ባቦ ወይም ስለ መልክዓ ምድሩ
vs
VS 'o


✅ባቦ የሚባለው የጌዴኦ የግብርና ሥርዓት በዩኔስኮ (UNESCO) በመመዝገቡ እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ!
✅ብዙዎች ባህላዊ መልክዓ-ምድር ፣ አግሮፎረስትሪ / ጥምር እርሻ የሚሉት በተባበሩት የባህልና የትምህርት ድርጅት/ዩኔስኮ በመመዝገቡ መላ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና በዉጪ በሀገሩ ውስጥ የምትኖሩ ሁሉ በዚህ ታሪካዊ ቀን እና ኩሩ ቀን በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ደስ አለን!

✅✅ሀገራችን የእራስ ያልሆነን ሥራ ተሻምተው የኔ ነው ማለት የተለመደ ሆኗል። ትናንት በዩኔስኮ በተመዘገበው ባቦንም ያስመዘገብነው እኛ ነን የሚሉትን እያየን ነው። ስለዚህ ማንም ሲናገር የነበረው ዕውነቱን እንድንመሰክር እግዚአብሔር ስላኖረን እንናገራለን።
አንድ የግብርና ሥርዓት አንድ ሰው ከመሬት ተነስተው ተናግሮ ወይም ደብዳቤ ፈርሞ ማስመዝገብ አይችልም።ምክንያቱም ሙያው ሊኖረው ስለሚገባው ነው።የጌዴኦ የግብርና ሥርዓት ኋላቀር ነው ሲባል የቆየ ነው። ቱሪስቶች ከመጡ ኋላቀርነቱን ለማየት እንጂ ለሌላ አይደለም ነበር።
✔️ጌዴኦ እግዚአብሔር በሰጠው ምድር የሚኖረው ነገር ግን መስራት የማይችል ሕዝብ ነው ሲሉ መስማት የተለመደ ነው። ልክ ነው ከእግዚአብሔር ተሰጥቷል ፣ ይሁን እንጂ ቁም ነገሩ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን ሁሉን ጠብቋል ወይ የሚለው ጥያቄ ነው።
✔️✔️ግብርና የሚደግፍ ቢሆንም በተለመደው የሚቃረን በመሆኑ የብዙዎች ራስ ምታት ነው።

ይቀጥላል:
# Jebo Tesfay
።።።።። ።።።።።።።።።።።።

ኋላቀር ነው ቢባልም በአንድ ካሬ ኪሎ ሜትር አንድ ሺህ 500 ሰው ማኖሩ ለዚያም ብዙ ሕይወቱ ፣ አፈሩ ፣ዉኃው ፣ አየሩ ፣ ሰው ወዘተ ተጠብቆ የብዙዎችን ራስምታት ነው። እንዲህ አይነቱ ሥርዓት ማነው የሚያስመዘግበው የኮንሶን እርከኖች ማስመዝገብ ቀላል ነበር ምክንያቱም እርከን በዘመናዊ ግብርና ሳይንስ የሚደገፍ ስለሆነ ነው። የጌዴኦ ሥርዓት ማስመዝገብ ከባድ ነበር ለምን ቢባል? _ስለሚሆን ይላሉ አባታችን።

✅✅አክለው ቀጠሉ እኔ የቀናኝ Agro Ecology የሚባል አዲስ ሳይንስ ስላጠናሁኝ ነው። ኋላቀር ነው ተብለው እንዲጠፋ ከተፈረደበት ሥርዓት ተወልጄ በውስጥ አድጌ ሀሮምያ ዩኒቨርስቲ ገብቼ። የዕጽዋት ግብርና አጠናሁ።

✅✅የጌዴኦ ባቦ ሥርዓት ከዘመን ግብርና #የተለየ መሆኑን የተረዳሁት ወደ ኔዘርላንድ ሀገር ሄጄ ክፍል የጌዴኦ ባቦ ሥርዓትን በፕ/ር ራኦልፍ ኦልድማን ስር በማጥናት ነበር።

የጥናቴን ውጤት Five thousands years of sustainability:(The case of Gede'o land use) በሚባለው መጽሐፌ ዓለም ሁሉ እንዲያነበው በonline አሳተምሁ።

✅✅ በመጽሐፌ መጨረሻ ያስቀመጥኩኝ የጌዴኦ ባቦ ሥርዓት በብዙዎች ሲባል እንደነበረው #ጊዜያችንን የቀደመ በመሆኑ ተመዝግቦ ዓለም ሁሉ እንዲማረው እንዲደረግ ያቀረብሁትን ሀሳብ መጽሐፌን በኢንተርኔት ያነበቡ የSLUF(Sustainable Land Use Forum) በመጀመሪያ ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው በዲላ ዩኒቨርስቲ አስተማሪ እና ከፍተኛ ተመራማሪ እና ከፍተኛ ከዞናችን የባህል በPhD ድግሪ በተመረኩበት መጨረሻ ላይ የጌዴኦን ሥርዓት መዝግቦ እንዲማርበት ያቀረብሁት ሀሳብ ተቀባይነት በማግኘት መጽሐፌን ከኢንተርኔት ያነበቡ ሰዎች የዛሬ 13 ዓመት ወደ እኔ መጥተው ሊረዱኝ ቃል ገቡ።

✍️✍️✍️ነገር ግን ለUNESCO የሰጠኹኝ አንድ መቶ ገጽ ጹሑፍ በመሠረቁ ፕሮጀክቱም እኔም ተረሳሁ😭😭። ጩኸቴን ቀምቶ ሲሄድ ሌባውን የጠየቁ አልነበረም ፣ እንዲያውም ብዙዎች ተባበሩት😭??።

ይቀጥላል።
B Lues Jebo Tesfaye
ጌዴኦ ገጽ / Gede'o page

የጥንት የጌዴኦ አባቶች ሀገር በቀል የስልጣኔ አሻራ የዓለም ቅርስ ሆኖ በዩኔስኮ መመዝገቡ የጌዴኦን ህዝብ ጥንታዊ የስልጣኔ ባለቤትነት ያረጋገጠ ነው፡፡
23/09/2023

የጥንት የጌዴኦ አባቶች ሀገር በቀል የስልጣኔ አሻራ የዓለም ቅርስ ሆኖ በዩኔስኮ መመዝገቡ የጌዴኦን ህዝብ ጥንታዊ የስልጣኔ ባለቤትነት ያረጋገጠ ነው፡፡

የጌዴኦ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ዮሴፍ ማሩ (ዶ/ር) የጌዴኦ ባህላዊ መልካዓምድር በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሣይንስና ባህል ድርጅት/UNESCO/ ላይ የዓለም ቅርስ ሆኖ በ...
18/09/2023

የጌዴኦ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ዮሴፍ ማሩ (ዶ/ር) የጌዴኦ ባህላዊ መልካዓምድር በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሣይንስና ባህል ድርጅት/UNESCO/ ላይ የዓለም ቅርስ ሆኖ በመመዝገቡ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

(ዲላ መስከረም 06/2016 ዓ/ም)የጌዴኦ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ዮሴፍ ማሩ (ዶ/ር) የጌዴኦ ባህላዊ መልካዓምድር በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሣይንስና ባህል ድርጅት/UNESCO/ ላይ የዓለም ቅርስ ሆኖ በመመዝገቡ ለመላው ኢትዮጵያውያንና ለዞኑ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።

በጌዴኦ ዞን ውስጥ የሚገኙትን የጌዴኦ ማሕበረሰብ የመሬት አያያዝ፣ ታሪካዊ ቅርሶች፣ ተክል ድንጋዮች፣ የዋሻ ላይ ጽሑፍና በባሕላዊ መንገድ ብቻ የሚተዳደሩ ደኖችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ጥረት ሲደረግ መቆየቱን የገለጹት ኃላፊው የመመዝገቡ ሂደት በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ዋጋ ከፍለው ሲንቀሳቀሱ ለነበሩ ባለድርሻ አካላት በዞኑ ህዝብ ስም ምስጋና አቅርበዋል ።

በቀጣይም ድርጅቱ በዞኑ ውስጥ ለሚሰራ ስራ የዞኑ ህዝብ አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ በመልክታቸዉ ጥር አቅርቧል ።

Amazing Cultural land scape of Gedeo zone
21/08/2023

Amazing Cultural land scape of Gedeo zone

Address

Dilla

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የጌዴኦ ጥምር እርሻ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የጌዴኦ ጥምር እርሻ:

Videos

Share