Debrebirhan Tourism Development Program

Debrebirhan Tourism Development Program Promoting Debirebirehan tourism potentials for the global business community ደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም
(1)

ጥቅምት 12 - የንጉሥ ሳህለሥላሴ ወሰንሰገድ የእረፍት እና የንጉሥ ኃይለመለኮት ሳህለሥላሴ የንግሥና መታሰቢያ ቀን … 175ኛ ዓመት መታሰቢያ ስም ጥሩና ገናናው የሸዋ ንጉሥ፣ ንጉሥ ሳህለሥላ...
22/10/2022

ጥቅምት 12 - የንጉሥ ሳህለሥላሴ ወሰንሰገድ የእረፍት እና የንጉሥ ኃይለመለኮት ሳህለሥላሴ የንግሥና መታሰቢያ ቀን … 175ኛ ዓመት መታሰቢያ

ስም ጥሩና ገናናው የሸዋ ንጉሥ፣ ንጉሥ ሳህለሥላሴ ወሰንሰገድ ያረፉት ከዛሬ 175 ዓመታት በፊት፣ ጥቅምት 12 ቀን 1840 ዓ.ም ነበር፡፡ ልጃቸው ንጉሥ ኃይለመለኮት ሳህለሥላሴ (የዳግማዊ አፄ ምኒልክ አባት) ሟቹን አባታቸው ዙፋን የተተኩትም ከዛሬ 167 ዓመታት በፊት፣ ጥቅምት 12 ቀን 1840 ዓ.ም ነበር፡፡

ንጉሥ ሳህለሥላሴ ወሰንሰገድ የራስ ወሰንሰገድ አስፋወሰን እና የወይዘሮ ዘነበወርቅ ጎሌ ልጅ ናቸው፡፡ የተወለዱት በ1788 ዓ.ም ነው፡፡ በዘመኑም ‹‹ኢትዮጵያን አንድ አድርጎ የሚገዛ ምኒልክ የሚባል ንጉሥ ይነግሣል›› የሚባል ንግርት ስለነበር፣ አባታቸው ራስ ወሰንሰገድ ‹‹ምኒልክ›› የሚል ስም አውጥተውላቸው ነበር። አባታቸው ራስ ወሰንሰገድ አስፋወሰን ሲሞቱ ሰኔ 1 ቀን 1806 ዓ.ም በ18 ዓመታቸው የአባታቸውን አልጋ ወርሰው ሸዋን ማስተዳደር ጀመሩ፡፡

ንጉሥ ሳህለሥላሴ ከሸዋ ባላባቶች መካከል (ከነጋሲ ክርስቶስ እስከ ኃይለመለኮት ድረስ ካሉት ገዢዎች መካከል) ኃያሉ፣ ሰፊ ግዛትና ብዙ ሀብት የነበራቸው እንደሆኑ ታሪካቸው ያሳያል፡፡ በወቅቱ በዓለም ላይ ኃያላን ከነበሩት ከብሪታኒያና ከፈረንሳይ መንግሥታትም ጋር የንግድና የወዳጅነት ስምምነት መፈራረማቸውም የዚሁ ኃያልነታቸው ማሳያ ነው፡፡

ንጉሥ ሣህለሥላሴ ሸዋ ገዢ በነበሩበት ጊዜ ኢትዮጵያ በዘመነ መሳፍንት አገዛዝ ላይ ትገኝ ስለነበር አንድ/ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት ባለመኖሩ እርሳቸው ኃይላቸውን በማጠናከር አንኮበርን መሰረት አድርገው ግሼ፣ ግድም፣ ኤፍራታ፣ አንጾኪያ፣ ይፋት፣ መርሐቤቴ፣ ላምዋሻ፣ ሞረት፣ እንሳሮ፣ አህያፈጅ፣ ቀይ አፈር፣ ቡልጋ፣ ምንጃር የተባሉትና አፋር ድረስ ያሉ ብዙ ቦታዎች በአስተዳደራቸው ስር እንዲሆኑ አድርገው ነበር።

ንጉሥ ሳህለሥላሴ በአስተዳደር ዘመናቸው የተቸገረን የሚረዱ፤ አቅም ላጣ ግብሩን የሚምሩ፤ ዕዳ ላለበት ዕዳውን የሚከፍሉ እንዲሁም ጥማድ በሬ ለሌለው ጥማድ እየሰጡ እረስ ቆፍር እያሉ ሕዝባቸውን ለሥራ የሚያበረቱ ነበሩ። እነዚህን በመሳሰሉ መልካም ሥራቻቸው የተነሳም በሕዝቡ ዘንድ በጣም ይወደዱ እንደነበር ታሪካቸው ያስረዳል።

የአሁኗ አዲስ አበባም ገና ከመመስረቷ በፊት ንጉሥ ሣህለሥላሴ መንግሥታቸውን (ግዛታቸውን) ለማስፋት በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ አሁን የምኒልክ ቤተመንግሥት ወደሚገኝበት አካባቢ መጥተው ድንኳን ተክለው በመቀመጥ ‹‹አንቺ ቦታ የልጅ ልጄ ትልቅ ከተማ ይቆረቁርብሻል … የልጅ ልጄ እዚች ቦታ ላይ ከተማ ይሰራባታል›› ብለው ትንቢት ተናግረው እንደነበር ይባላል። ይህ ትንቢታቸውም የልጅ ልጃቸው በሆነት ንጉሰ ነገሥት ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ፍጻሜ አገኘ (እውን ሆነ)።

በመጨረሻም ንጉሥ ሣህለሥላሴ ለ33 ዓመታት ከ 5 ወራት ያህል ሸዋንና በሸዋ ዙሪያ ያለውን ቦታ ሲያስተዳድሩ ቆይተው ከዛሬ 175 ዓመታት በፊት (ጥቅምት 12 ቀን 1840 ዓ.ም) ደብረ ብርሃን ከተማ ላይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ስርዓተ ቀብራቸውም ራሳቸው ባሰሩት በአንኮበር ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል።

የንጉሥ ሳህለሥላሴን ሞት ተከትሎ ዙፋኑን የወረሱት ልጃቸው ንጉሥ ኃይለመለኮት ሳህለሥላሴ ነበሩ፡፡ የንጉሥ ኃይለመለኮት እናት ወ/ሮ በለጥሻቸው ወልዴ ይባላሉ፡፡

ንጉሥ ኃይለመለኮት በሰውነታቸው ግዝፈትና ጥንካሬ እንዲሁም በልባቸው ቀናነት በሸዋ ዘንድ የታወቁና የተወደዱ ንጉሥ ነበሩ። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ ‹‹የኢትዮጵያ ታሪክ›› በሚለው መጽሐፋቸው እንደሚነግሩን ንጉሥ ኃይለመለኮት ከጥንካሬያቸው የተነሳ ኢላማ ተኩስ በሚተኩሱ ጊዜ መሳሪያውን አጠንክረው በመያዛቸው ምክንያት ጥይቱ ሲወጣ ጠመንጃቸው ለሁለት ተሰብሮ እጃቸው ላይ ቀርቶ ያውቃል።

ንጉሥ ኃይለመለኮት ሸዋን ለ8 ዓመታት አስተዳድረዋል። በስልጣን ላይ ሳሉም ተቀናቃኝ ሊሆኑባቸው የሚችሉትን ወገኖቻቸውን እንዲያስሯቸውና እንዲያስወግዷቸው ሰዎች ሲመክሯቸው፣ ‹‹ተዉ! ይሄን አላደርገውም! እግዚአብሔር የወደደውን ነው የሚያስገዛው›› የሚሉ ቀና ሰው እንደነበሩ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ በመጽሐፋቸው ጠቅሰውታል።

በመጨረሻም ዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ በሀገሪቱ በየቦታው ያለውን የተከፋፈለ አገዛዝ ወደ አንድ አስተዳደር በማምጣት በማእከላዊ መንግሥት ስር የምትተዳር አንዲት ሀገር ለመመስረት አስበው ከየመሳፍንቱ ጋር በሚዋጉበት ጊዜ ‹‹ንጉሰ ነገሥቱ ወደ ሸዋም ሊመጡ ነው›› የሚል ወሬ ተሰምቶ ንገሥ ኃይለመለኮትም ለጦርነት ተዘጋጁ፤ ሆኖም ግን ከጦርነቱ ቀደም ብሎ ንጉሥ ኃይለመለኮት ታመው ነበርና እርሳቸው በጦርነቱ ሳይካፈሉ፣ ጥቅምት 30 ቀን 1848 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡

(ልዑል አምደ ፅዮን)
(የደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም)

የንጉሥ ሳህለሥላሴ ወሰንሰገድ ቤተመንግስት ግንባታ ፕሮጀክትና ታሪክከአንበሳ ውድምና ድልነዓድ ወደ መካከለኛው የኢትዮጵያ ክፍል የተሰበሰበው መንበረ-መንግስት፣ ፖለቲካና የዕውቀት ማዕከል ሸዋ ...
16/10/2022

የንጉሥ ሳህለሥላሴ ወሰንሰገድ ቤተመንግስት ግንባታ ፕሮጀክትና ታሪክ

ከአንበሳ ውድምና ድልነዓድ ወደ መካከለኛው የኢትዮጵያ ክፍል የተሰበሰበው መንበረ-መንግስት፣ ፖለቲካና የዕውቀት ማዕከል ሸዋ ላይ ዓለት ቆፍሮ፣ ወጋግራ ወድሮ ተመሰረተ።

በንጉስ ዐምደጽዮን የኢትዮጵያን ደጆች ከጠላትና ከብተና እያዳነ፣ በአፄ ዘርዓ ያዕቆብ የተከፈተ የዕውቀትና ምርምር በር፣ በአፄ ልብነድንግል ተሟሽቶ በአቤቶ ያዕቆብ መንገድ የፀናች አገር፣ በወይዘሮ ዘነበወርቅ ሐረግ በወሰንሰገድ ማዕረግ ጌጥ ተሸልሞ ንጉሥ ሣሕለሥላሴ ወሰንሰገድ ላይ ይደርሳል።

ንጉሥ ሣሕለሥላሴም በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በንግስና ዘመኑ ፍትሐዊ ፍርድን፣ ዘመናዊት ኢትዮጵያን በመፍጠርና የኤኮኖሚ ፖሊሲ በመንደፍ ከታጆራ እስከ አንኮበር ከዚያም እስከመካከለኛው አፍሪካ ረጅም ንግድ አስፋፍቷል።

በወቅቱም ከአምኃየስ ቀጥሎ አንኮበርን እና ደብረብርሃን-አንጎለላን የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ማዕከል በማድረግ ንጉሥ ሣሕለስላሴ ትልቅ ሚና ተጫውቷል።

ይሕ አንጎለላ የሚገኘው ፍርስራሽ ቤተ መንግስት ወደ ጅሑር መሥመር በሚወስደው መንገድ 10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል።

ቤተ መንግስቱ በ1487 ዓ.ም ዐፄ ናዖድ ባስገነቧት የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ግቢ የሚገኝ ሲሆን፣ የታላቁ የአድዋው የጦር ጀግና ራስ መኮንን እናት ወይዘሮ ተናኘወርቅ፣ ራስ ዳርጌ እና የዳግማዊ ዐጤ ምኒልክ አባት ንጉሥ ኃይለመለኮት የተወለዱበትና ወጣትነታቸውን ያሳለፉበት ቅጥር ነው።

ንጉሥ ሣሕለሥላሴ ከ1830-1848 ከነገሡት የፈረንሳይ ንጉሠ ነገሥት ሉዊስ ፊሊፕ የተበረከተለትን ስጦታ የተረከበበት፣ እንዲሁም ንጉሡ ለዓለም-አቀፍ ንግድና ትብብር ትልቅ ምልከታ ስለነበረው ህዳር 7 ቀን 1834 ዓ.ም ከፈረንሳይ መንግስት እና ግንቦት 28 ቀን 1834 ዓ.ም የቦምቤይ ገዢ ከነበሩት ካፒቴን ዊሊያም ወኪልነት በታላቋ ብሪታንያ ንግስት ቪክቶሪያ ስም በአንድ ዓመት ውስጥ ሁለት የንግድና ወዳጅነት ስምምነት የተፈራረመበት ቦታ ሸዋ-አንጎለላ የሚገኘው ይሕ ቤተ መንግስት ነው።

ቤተ መንግስቱ ዛሬም ሕያው ምስክር አሻራዎች ያሉት፣ የንጉሡ እልፍኝና አዳራሽ፣ የተዋጊ ፈረሶች ካምፕ፣ የግብር አዳራሽና የምድረ-ግቢው መውጫና መግቢያ ዕድሞ ፍርስራሽ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።

የደብረብርሃን ከተማም ወደ ሪጅዮፖሊታን የከተማ ደረጃ በማደጉ ቅርሱ ከሐምሌ 1 ቀን 2014 ጀምሮ በከተማ አስተዳደሩ ሥር እንዲገቡ ከተደረጉ የቱሪስት መስሕቦች አንዱ ሲሆን የመዳረሻ ልማት ዕቅድ አካል ሆኖ ንቅናቄ ተጀምራል።

ይህ የመዳረሻ ልማት የአካባቢውን ማሕበረሰብ በማሳተፍ የኤኮኖሚ መሠረት እንዲሆን ሁሉም እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቧል።

(የደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም)

የአልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን ‹‹ንጉሥ››ነት - መስከረም 27 ቀን 1921 ዓ.ምአልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ መኮንን ወልደሚካኤል ራሳቸውና ደጋፊዎቻቸው ባቀናበሩት ፖለቲካዊ ሴራ ምክንያት የ‹‹ንጉሥ...
07/10/2022

የአልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን ‹‹ንጉሥ››ነት - መስከረም 27 ቀን 1921 ዓ.ም

አልጋ ወራሽ ራስ ተፈሪ መኮንን ወልደሚካኤል ራሳቸውና ደጋፊዎቻቸው ባቀናበሩት ፖለቲካዊ ሴራ ምክንያት የ‹‹ንጉሥ››ነት ማዕረግ የጨበጡት ከዛሬ 94 ዓመታት በፊት (መስከረም 27 ቀን 1921 ዓ.ም) ነበር፡፡

መስከረም 17 ቀን 1909 ዓ.ም የዳግማዊ አጤ ምኒልክ አልጋ ወራሽ የነበሩት ልጅ ኢያሱ ሚካኤል ከስልጣን ተሽረው ዘውዲቱ ምኒልክ ንግሥት (ንግሥተ ነገሥታት)፣ ተፈሪ መኮንን ደግሞ አልጋ ወራሽ ከሆኑ በኋላ አልጋ ወራሹ በትንቢት የተነገረላቸውንና እርሳቸውም ያልሙት የነበረውን ‹‹ንጉሰ ነገሥትነታቸውን›› እውን ለማድረግ በምስጢርም በገሃድም ብዙ ተግባራትን ፈፅመዋል፤ አስፈፅመዋል፡፡

ዳግማዊ አጤ ምኒልክ የሾሟቸውን ሚኒስትሮች በተለያዩ ዘዴዎች በማዳከም የንግስቲቱን ሥልጣንና ተሰሚነት ወደራሳቸው ጠቀለሉት፡፡ ከንግሥቲቱ ጋር የነበራቸውም ልዩነት/አለመግባባት ገሃድ ወጣና በሽማግሌና በመልዕክተኛ ብቻ መገናኘት ጀመሩ፡፡

በስልጣን እንኳ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የነበሩት የተፈሪ መኮንን ደጋፊዎች በአልጋ ወራሹ ፖለቲካዊ ድሎች የልብ ልብ እየተሰማቸው መጣና፣ ‹‹ተፈሪን ያንግሱልን›› የሚል ጥያቄ ለንግሥቲቱ አቀረቡ፡፡ ለወትሮውም ቢሆን የዋህነቱና ደግነቱ ላይ እንጂ ፖለቲካዊው ሴራና ምስጢር የማይገባቸውና የማይሆንላቸው የእምዬ ልጅ፣ ሁሉም ነገር ከእጃቸው ወጥቶ ስለነበርና አማራጭም ስላልነበራቸው፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ብዙም ያልተለመደውን ንጉሥ/ንግሥት እያለ/ች ተደራቢ ንጉሥ/ንግሥት የሚሾምበትን አሰራር ‹‹እሺ … ንጉሥ ብየዋለሁ›› ብለው ፈቀዱ፡፡

አልጋ ወራሹም መስከረም 27 ቀን 1921 ዓ.ም ‹‹ንጉሥ›› ሆኑ፡፡ ይኸውም አልበቃቸው ብሎ፣ ‹‹የንግሥ በዓሉ በቤተ-ክርስቲያን ይሁንልኝ›› አሉ፡፡ ንግሥቲቱ በሃሳቡ እንደማይስማሙ ተናገሩና አማካኝ ቦታ ተመርጦ የንግሥ በዓሉ ተከናወነ፡፡
ከዚህ ጊዜ በኋላ የዳግማዊ አጤ ምኒልክ ልጅ (ዘውዲቱ ምኒልክ) እና የአክስታቸው የልጅ ልጅ (ተፈሪ መኮንን) ተያይተው አያውቁም ይባላል፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት በአንድ ቤተ-መንግሥት ይደረግ የነበረው የግብር ማብላት ስርዓት ቀርቶ ‹‹ላይኛው ቤተ-መንግሥት›› እና ‹‹ታችኛው ቤተ-መንግሥት›› እየተባለ በሁለት አብያተ-መንግሥታት ሆነ፡፡ ሹማምንቱም ለሁለት ተከፈሉ፡፡ ሌላም ሌላም …

[መቼም ልጅ ኢያሱ በተሻሩበትና ተፈሪ መኮንን ‹‹ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ›› ተብለው ንጉሰ ነገሥት በሆኑበት ጊዜያት መካከል ያሉት ዓመታት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለም የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ፖለቲካዊ ሴራና ሽኩቻ የታየባቸው ዓመታት እንደሆኑ መገንዘብ ይቻላል፡፡

(ልዑል አምደፅዮን)

የልቼ ቤተመንግሥት ግንባታ
04/10/2022

የልቼ ቤተመንግሥት ግንባታ

ወጣቱ ምኒልክ መቅደላ ገብተው በቁም እሥር በነበሩበት ጊዜ ከዐጤ ቴዎድሮስ ልጅ ከመሸሻ ጋር አብረው ነው ያደጉት። ወዲያውም የደጃዝማችነት ማዕረግ ተሹመው በጥር ወር 1856 ዓ.ም የዓፄ ቴዎድ...
04/10/2022

ወጣቱ ምኒልክ መቅደላ ገብተው በቁም እሥር በነበሩበት ጊዜ ከዐጤ ቴዎድሮስ ልጅ ከመሸሻ ጋር አብረው ነው ያደጉት። ወዲያውም የደጃዝማችነት ማዕረግ ተሹመው በጥር ወር 1856 ዓ.ም የዓፄ ቴዎድሮስን ልጅ ወይዘሮ አልጣሽን አገቡ። በዚህ ሁኔታ እስከ 22 ዓመታቸው ድረስ ለአሥር ዓመታት ዐፄ ቴዎድሮስ ግቢ ኖሩ።

ዐፄ ቴዎድሮስ ምኒልክን እንደልጃቸው ያዩዋቸውና በታላቅ ጥንቃቄም ያስተምሯቸው ነበር። ምኒልክም ቴዎድሮስን እንደአባት ይወዷቸው እንደነበር ይገለጻል። ሆኖም የአጤ ቴዎድሮስ የዘመናዊነት ትልም ይሰምር ዘንድ ምኒልክ በአባቱ መንበር መንገስ ነበረበትና በሊቁ አዛውንት ደጃዝማች ገርማሜ አማካሪነት ከመቅደላ ሰኔ 24 ቀን 1857 አምልጠው አንኮበር ገቡ።

በአንኮበር ጥቂት ወራት ከተቀመጡ በኋላ ወደ ደብረ ብርሃን ወጥተው አዲሱን ከተማቸውን ልቼን እያሠሩ ተቀመጡ።

ዐፄ ምኒልክ የመጀመሪያ ቤተ መንግሥታቸው ልቼ እንደነበረ የታሪክ ድርሳናትና የልቼ ቤተ መንግሥት ፍርስራሽ ያስረዳል። በተለይም ዐፄ ምኒልክ ከየካቲት 1870 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 1878 ዓ.ም በልቼ ቤተመንግሥት እንደነበሩ በተጻጻፉት ደብዳቤ አማካኝነት ታውቋል።

ኤስ ሩቬንደንና ሪቻርድ ፓንክረሥት እንደመዘገቡት በመጋቢት 1878 ዐፄ ዮሐንስና ዐፄ ምኒልክ ታሪካዊው ቦታ ላይ የልቼ ስምምነት እየተባለ የሚጠቀሰውን ስምምነት እዚህ ቦታ ተፈራረሙ። ጸሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ ታሪከ ነገስት ዘዳግማዊ ምኒልክ በተሰኘው መጽሐፋቸው የዐጼ ምኒልክን ንግሥናና የልቼ ቤተ መንግሥትን ሥነ ሥርዓት እንዲህ ይገልፁታል፣

ምኒልክ መስቀል በዓልን ውለው ልቼ ከተማቸው ወጡ። ከዚያም በሥርዓተ መንግሥት ዘውድ የሚደፉበት፣ አዳራሽ የሚገኙበት ጊዜ ነውና ልቼ ከተማ ከዕድሞው ግቢ ሰፊ ዳስ ተሠርቶ ግብር ለማብላት ልክ መጠን የሌለው ሁኖ ተዘጋጅቶ ነበረ። ደግሞም ከዳሱ አፋፍ ከሰገነቱ ዝቅ ያለ ሥራው ልዩ ልዩ የሆነ መንበር ተሠርቶ ነበር። በዚህም ጊዜ የዳሱ ጌጥ ሥራው የቆመበትም ሁሉ በልዩ ልዩ ዓይነት ግምጃ የተሸፈነ ነበር። ከዚህም አስቀድመው ባዋጅ ‘በምገዛው አገር የሚኖር ካህን ከየደብሩ መስቀልና ጽና ከአልባሳቱ ጋር እየያዘ በጥቅምት ሁለት ቀን ይግባ’ ብለው አዘውት ጠቅሎ ገባ።

ከዚህም በኋላ በጥምቅት 3 ቀን ቅዳሜ ማታ ንጉሥ ከነሠራዊታቸው ከልቼ ተነሥተው ደብረብርሃን ወርደው አደሩ። ሲነጋ ንጉሡ ልብሰ መንግሥት ለብሰው መምህር ገብረሥላሴ፣ መምህር ግርማ ሥላሴ ንጉሡን በወርቅ አልጋ አስቀመጧቸው፤ ዘውዱንም ደፉላቸው።

ራስ ዳርጌና ራስ ጎበና የራስወርቅ አሥረው አብረው ወጡ። ባለወርቅ መጣምር በቅሎዎቻቸውም ላይ ተቀምጠው ንጉሡን በማጀብ የ20ኛው ክፍለ-ዘመን ፅኑ ኢትዮጵያ ቁልፍ የታሪክ አንጓ መጀመሩን አበሰሩ።

ይሁን እንጂ ይህ ታላቅ ሥፍራ ለምቶ የጎብኚዎች መዳረሻ ባለመሆኑ እየተዘነጋ መጥቷል። የቤተመንግስቱም ፍርስራሽና ልዩ ልዩ ክፍሎቹ ከጥበቃ ጉድለት ችግር ላይ ይገኛል።

በግቢው ፍርስራሾች፣ ነባሩ ካብ ግንብ እና የምኒልክ ምንጭ እና የበዛብሕ መካነ-መቃብር ይገኝበታል።

እነዚህን እና ሌሎች ታሪካዊ ቦታዎች መልሶ በማልማት የቱሪዝም ልማት ሥራው አካል በማድረግ የደብረብርሃን ከተማ ባሕልና ቱሪዝም መምሪያ ዓለም-አቀፍ የፕሮሞሽንና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ነድፎ እየሠራ ይገኛል።

(የደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም)

03/10/2022

# የመስቀል #በአል #ልዩ #ፕሮግራም "ዘርያዕቆብ የዘራው ጥበብ" የመስቀል በአል ልዩ ፕሮግራም ! በርኖስ ጥበብ Vellum is writing. Vellu...

ሸዋ የንጉሥ እራት ለቱሪዝም ልማት ልዩ  መሠናዶ!
02/10/2022

ሸዋ የንጉሥ እራት ለቱሪዝም ልማት

ልዩ መሠናዶ!

እንኳን ወደ ታላቁ ወርቃማ ጉዞ ይፋዊ የYouTube ቻነል በሰላም መጣችሁ!

በድጋሜ እንኳን አደረሳችሁ!ሸዋ የንጉሥ እራት ለቱሪዝም ልማት  የተሰኘው ልዩ የቴሌቭዥን ዝግጅታችን ረፋድ ላይ ሳትከታተሉ ያለፋችሁ በድጋሜ ዛሬ ምሽት ከ 5:15 ጀምሮ እንዲሁም  ነገ ረፋድ ...
27/09/2022

በድጋሜ እንኳን አደረሳችሁ!

ሸዋ የንጉሥ እራት ለቱሪዝም ልማት የተሰኘው ልዩ የቴሌቭዥን ዝግጅታችን ረፋድ ላይ ሳትከታተሉ ያለፋችሁ በድጋሜ ዛሬ ምሽት ከ 5:15 ጀምሮ እንዲሁም ነገ ረፋድ ከ 4:30 ጀምሮ በአርትስ ቴሌቭዥን ሥለሚተላለፍ መከታተል ትችላላችሁ።

(የደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም አድቫይዘሪንግ ቦርድ)

እንኳን ለብርሃነ መሥቀሉ በሠላም አደረሳችሁ።ሸዋ የንጉሳውያን የእራት ምሽትና የገቢ ማሰባሰቢያ ልዩ ዝግጅት፣ በእለተ መሥቀል ከረፋዱ 3:00- 4:30 በአርትስ ቴቪ ይተላለፋል።ልክ እንደንጉሳ...
26/09/2022

እንኳን ለብርሃነ መሥቀሉ በሠላም አደረሳችሁ።

ሸዋ የንጉሳውያን የእራት ምሽትና የገቢ ማሰባሰቢያ ልዩ ዝግጅት፣ በእለተ መሥቀል ከረፋዱ 3:00- 4:30 በአርትስ ቴቪ ይተላለፋል።

ልክ እንደንጉሳውያኑ የእልፍኝ አመሻሽ በቤታችሁ ድምቅ ብላችሁ እንድትከታተሉ ተጋብዛችኋል።

መልካም በዓል!

(የደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም)

እንኳን ለዚህ ታላቅ በዓል ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ።~ክቡራንና ክቡራት የውዲቷ ከተማችን የደብረ ብርሃን ነዋሪዎች ይህንን ታላቅ የመስቀል በዓል ለማክበር በዚህ ታላቅ አደባባይ የተ...
26/09/2022

እንኳን ለዚህ ታላቅ በዓል ለብርሃነ መስቀሉ በሠላም አደረሳችሁ።

~ክቡራንና ክቡራት የውዲቷ ከተማችን የደብረ ብርሃን ነዋሪዎች ይህንን ታላቅ የመስቀል በዓል ለማክበር በዚህ ታላቅ አደባባይ የተሰበሰባችሁ ሁላችሁም ከሰይጣን እስራት ነፃ የወጣንበት ድንቅ ምስጢር የተፈፀመበትን በዓል እናከብር ዘንድ ትናንትን አሳልፎ መልካም እድሜ ሰጥቶ ዛሬን እንድናይ ለረዳን አምላክ ፍፁም ምስጋና ይገባዋልና የአምላካችን ስሙ ለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁን።

~ሸዋ ደብረ ብርሃን በነ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ ሁሉን አስማምቶ በያዘ የታመነ የህዝብ አገልግሎት በነ እምዬ ምኒልክ ደጋግ ኢትዮጵያውያን ነገሥታት አስቀድማ የተሰራች የከበረች ምድር የረጅም ጊዜ ጥንተ ታሪክ ያላት ሸዋ ውቢቱ ከተማችን ደብረ ብርሃን ልክ እንደ ስሟ ብርሃን የሆነላት በሃይማኖት አባቶች ፀሎት እየተጠበቀች የከበረ ስሟና ታሪኳ በጎ ሥራዋም ሳይደበዝዝ ዛሬ መስቀሉን ከመላው ልጆቿ ጋር ተውባ ልታከብር የተሰናዳች እመቤትን መስላ ስናያት በሁላችን ልብ ውስጥ ሐሴትን ይሞላል። ደብረ ብርሃን ከሰማይ የወረደ ብርሃንም ተጎብኝታለች ይህንን መነሻ አድርገው የብርሃን ተራራ ደብረ ብርሃን አሏት የሰማይ ምስጢር የተከናወነባት መንፈሳዊት ከተማ ደብረብርሀን የአፄ ዘርዐ ያዕቆብ ፋና የእምዬ ምኒልክ የክብር ዙፋን

~ይህች ጥንታዊትና ታሪካዊት ከተማችን ደብረ ብርሃን መስቀሉ ገብቷታል የቅዱስ መስቀሉም ዙፋን ሆናለች አሸናፊው እግዚአብሔር የዓለማት ጌታ የሰላም አለቃ የሁሉ ገዥ መድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ተሰቅሎ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ 5500 ዘመን ሙሉ በዲያቢሎስ እስራት ተይዞ የነበረውን የአዳም ዘር ነፃ የወጣበት የአለም ሁሉ ብርሃን ሰይጣንን ድል መንሻ ጋሻችን መስቀል በዛሬው ዕለት ሲከበር የመስቀሉን አገልግሎትና ቅድስና በመረዳት ነው።

~ለ5500 ዘመናት የሰው ዘር በሙሉ በኃጢአት ሰንሰለት ታስሮና በድቅድቅ ጨለማ ተውጦ በነበረበት ዓመተ ፍዳ እግዚአብሔር ወልድ ለዓለም ድኅነት የተሰዋበት መስቀሉን የዓለም ብርሃን የቤተክርስቲያን መሠረት ነው" እያልን እናስታውሰዋለን።

~እንደሚታወቀው ያኔ በዕለተ ዓርብ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቀኑ በዘጠኝ ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው በገዛ ሥልጣኑ ከለየ እና በትንሣኤው ከሞት በ፫ኛው ቀን ሲነሣ ተሰቅሎ የነበረበት የእንጨት መስቀል ሌት ተቀን በሙሉ ሳያቋርጥ እንደፀሐይ አበራ፡፡ የመስቀሉ ኃይልም አጋንንት ሲያባርር፣ ድውይ ሲፈውስና ሙት ሲያነሣ ሲያዩ ቤተ እሥራኤል አይሁድ በቅናት ተነሥተው በዓዋጅ ትልቅ ጉድጓድ በመቆፈርና በመቅበር የቤት ጥራጊና አመድ የቆሻሻ መከማቻ አደረጉት፡፡

~በዚያን ጊዜም የታላቁ ቆስጠንጢኖስ እናት ንግሥት እሌኒ የተባለች ደግ ሴት የጌታችን ኢየሱስ መስቀል መስከረም ፲፯ ቀን ፫፻፳ ዓ.ም. ላይ በዕጣን ጢስ ምልክት ቁፋሮ አስጀምራ መጋቢት ፲ ቀን አገኘችው፡፡ ዛሬም ያን ምሳሌ በማድረግ ደመራውን እንዲህ ደምረን በዓሉን እናስበዋለን። ንግስት እሌኒ መስቀሉንም በማውጣት ታላቅ ቤተ መቅደስ ጎልጎታ ላይ ሠርታ በክብር አስቀመጠችው፡፡ ይህ መስቀልም ከዚያ ዘመን ጀምሮ እንደ ፀሐይ እያበራ፣ ድውይ እየፈወሰ፣ አጋንንት እያባረረ፣ ሙት እያነሳ፣ ዕውራንን እያበራ ብዙ ተአምራትን አደረገ፡፡ ስለዚህም በየዓመቱ የመስቀልን በዓል ስናከብር ደመራ የምንደምረውና የምናበራው ንግሥት ዕሌኒን አብነት በማድረግ ነው።

~ንግስቲቱ እሌኒ ያገኘችው መስቀል ወደ ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ መጥቶ በክብር መቀመጡን ባሰብን ጊዜ ደግሞ ደስታችን ሙሉ ነው። የቅዱስ መስቀሉ ወደ ሀገራችን የመምጣቱ ነገር ሲነሳ ሸዋ ደብረ ብርሃን ቀዳሚውን ታሪክ ትይዛለች የነገስታት ስር የሆነችው ሸዋ ደብረብርሃን በአፄ ዳዊት ልጅ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ አማካኝነት መስቀሉን በክብር ተቀብላ አሳርፋለች። አፄ ዘርዐ ያዕቆብ በመናገሻ ከተማቸው በደብረ ብርሃን ላይ ቤተ መቅደስ ሠርተው ለማስቀመጥ ሲጥሩ "ወዳጄ ዘርዐ ያዕቆብ ሆይ! መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ›› የሚል መልእክት በራእይ ተነገራቸው፡፡ ንጉሡም በኢትዮጵያ አውራጃዎች ሁሉ መስቀለኛ ቦታ በመፈለግ ከብዙ ቦታ ላይ አስቀምጠውት ነበር፡፡ ነገር ግን የመጨረሻውን ቦታ ያላገኙ በመሆኑ በራእይ እየደጋገመ ‹‹መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ›› እያለ ይነግራቸው ነበር፡፡

~በቤተክርስቲያኒቱ የታሪክ ትምህርት መሠረት ዓፄ ዘርዐ ያዕቆብም ለ፯ ቀናት ያህል ሱባዔ መግባታቸው ይነገራል በዚያም መስቀልኛውን ቦታ በብርሃን ዓምድ እየተመሩ፤ ወደ ወሎ ክፍለ ሀገር አምባሰል አውራጃ ውስጥ ግሸን ከምትባል ስፍራም መርቶ አደረሳቸው፡፡ በርግጥም ይህች ግሽን የተባለች አምባ ጥበበኛ ሰው እንደቀረፃት የተዋበችና መስቀልኛ ቦታ ሁና ስለአገኟት የልባቸው ስለደረሰ ደስ አላቸው፡፡ በዚያችም አምባ ታላቅ ቤተ መቅደስ ሠርተው መስቀሉንና ሌሎች አብረው የመጡትን ንዋያተ ቅድሳት በየማዕረጋቸው የክብር ቦታ መድበው አስቀመጧቸው።

~ክቡራንና ክቡራት የውዲቷ ከተማችን የብርሃን ተራራ ተብላ የምትጠራው የደብረ ብርሃን ልጆች ከተማ አስተዳደራችን ይህንን ታሪክ በጥቂቱ ለማስታወስ የወደደበት ምክንያት ታሪኩ ሙሉ የደብረ ብርሃን መልኳ ስለሆነ ከተማ አስተዳደሩም ሆነ በደብረ ብርሀን ከተማ በውስጧ ያሉ ነዋሪዎች እንዲሁም ዓለም በሙሉ ለታሪኩ የሚገባውን ክብር ይሰጠው ዘንድ ነው እንደ ከተማችን የዚህ ትልቅ ታሪክ ኃላፊነት እንዳለብን ይሰማናል። ደብረ ብርሃን የቅዱስ መስቀሉ ማደሪያ ሆና አገለገለች ከሸዋ ተነስቶ ወሎ በዚያ የማር አንባ ከመስቀለኛው ቦታ ግሸን ደብረ ከርቤ የማደሩን ነገር ስናስብ ደግሞ በብዙ መልኩ እንረዳዋለን።

~በቀደሙት ደጋግ አባቶቻችን ዘንድ ወሰን ሳይገድባቸው ዘር ሳይከፍላቸው ቋንቋ ሳይለያቸው ከኢትዮጵያ ጫፍ እስከ ጫፍ ድረስ ለሀገር አንድነት ዋጋ የከፈሉ በመልካም አገልግሎታቸው የምናስታውሳቸው አባቶቻችን ዘንድ ፈፅሞ ዘረኝነት የለም። በታላቁ ንጉሥ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘንድ ዘረኝነት ቢኖር ኖሮ ቅዱስ መስቀሉ በዚሁ በደብረ ብርሃን ተወስኖ ይኖር ነበር ነገር ግን አፄ ዘርዐ ያዕቆብ በዚህ ዝቅ ሳይሉ በታላቁ ተራራ በመስቀለኛው ስፍራ በግሸን ደብረ ከርቤ ቤተመቅደስ ሰርተው መስቀሉን በዚያ አኑረው መላው ኢትዮጵያንና ዓለሙን በሙሉ ይባርክ ዘንድ ይህንን አደረጉ። ደብረ ብርሃን አፄ ዘርዐ ያዕቆብን የወለደች ደገኛውን ንጉስ ያስገኘች የነገስታት እናት የቅዱሳን መካናት መንበር ስለሆነች በዚሁም እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እወዳለሁ።
~አይሁዳውያን በዘመኑ ቅናት አድሮባቸው መስቀሉን ቢቀብሩትም እውነት ተቀብሮ ስለማይቀር ለረጅም ዘመናት ተቀብሮ የኖረው መስቀል በእሌኒ አማካኝነት ከተቀበረበት ወጥቷል መስቀሉ እውነት ነው መስቀሉ መድኃኒት ነው መስቀሉ ኃይል ነው መስቀሉ ሰላም ነው ስለዚህ እውነትና ሰላም ኃይልና መድኃኒት ፈፅሞ መቀበር የለበትምና ከመቃብር ወጣ። ምቀኞች አይሁዳውያን ተባብረው ቅዱስ መስቀሉን ሸሽገው በመቃብር ደብቀው ቢያኖሩትም መስቀሉ አሸናፊ ሆኖ እንዲህ የመሰባሰባችን ምክንያት ሆኗል። ዛሬም እንደ ጥንቱ አይሁዳውያንን የሚመስሉ ምቀኞች በሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ ያኔ በመስቀሉ ላይ እንደተደረገው ዓይነት በደል ሊያደርሱ የተዘጋጁ ክፉዎች ቢኖሩም ኢትዮጵያ ሀገራችን ልክ እንደ መስቀሉ የጠላትን ክፉ ሐሳብ እያመከነች የምትቀጥል ይሆናል ይህም የሚሆነው እንደ ንግስት እሌኒ ዐይነት ሴቶች ሲኖሩ ነው ደግሞም እንደ ደጉ አባት አፄ ዘርዐያዕቆብ ዐይነት ትውልዶች ሲኖሩ ነው የዚህን ጊዜ ዓለም በሙሉ ከኢትዮጵያ ላይ ፊቱን ቢያዞርም እንደመስቀሉ ያለ የማይነጥፍ ታሪኳ ከነ ክብሩ ይቀጥላል ማለት ነው። ምዕራባውያን ለረጅም ዓመታት የኢትዮጵያን እንደ አልማዝና ዕንቁ የከበረ ታሪኳን ቆሻሻቸውን እየደፉ የመለያየት የመከፋፈል የጥርጥር ጥራጊያቸውን እየጣሉ ሊቀብሩት የረጅም ጊዜ ጥረት አድርገዋል ነገር ግን በየዘመኑ የተነሱ እሌኒን የሚመስሉ የኢትዮጵያ ሴቶች አፄ ዘርዐ ያዕቆብን የሚመስሉ ጀግናና ደጋግ ወንዶች ብርቱ ትግል የጠላት ሐሳብ እየመከነ ሀገራችን ከዛሬ ደርሳለች።

~ዛሬም የወዲቷ ከተማችን የሸዋ ደብረ ብርሃን ልጆች እንደ ቀደሙት አባቶቻን ታሪክ ዝቅ ሳትሉ እንደ ጥበበኛው ንጉሥ አፄ ዘርዐ ያዕቆብ በጥበብ የምንገለጥ ልንሆን ይገባል እኛ ታሪካችን ሰፊ ነው አፄ ዘርዐ ያዕቆብን ስናስብ በመላው ኢትዮጵያ የበዛ ታሪካቸውን እንጂ በደብረብርሃን የመወለዳቸውን ነገር ብቻ አንሰብክም ዛሬም ያለን የነገሥታቱ ልጆች በሸዋ ደብረ ብርሃን ብቻ ታጥሮ ያለ ታሪክ አይደለም ያለን በመላው ኢትዮጵያ የሚነገር እንጂ።

~በመሆኑም ዛሬ ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ አይሁድ ምዕራባዎያን የሚያደርጉባትን ሁለንተናዊ ጫና ለመዋጋት የአፄ ዘርዐ ያዕቆባዊነትን መንፈስ መያዝ ይገባል ምኒልካዊነትንም ማንገብ ይገባል። በሀገራችንም ያሉ የእናት ሆድ ዥንጉርጉር እንዲሉ ከእናት ኢትዮጵያ ማኅፀን የተገኙ ልጆችም ለዚች መልካም እናት ጦር ሰብቀውባታል ከጠላት ጋር ተማክረው የሚችሉትን ሁሉ አድርገዋል። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ለጠላት እጅ ሰጥቶ የማያውቀው ድንቅ ታሪኳ ከእርሷ ጋር ነውና ታሸንፋለች። መስቀሉ ከመቃብር ወጥቶ ዛሬም ድንቅን ያደርጋል አይሁዳውያን ግን ሞተው ተቀብረዋል ክፉ ታሪካቸው እስካሁን ድረስ ይነገራል ኢትዮጵያም እያሸነፈች ጠላቶቿም እየተቀበሩ በለተመደው አስገራሚ ታሪኳ ትቀጥላለች ማለት ነው። እንጨቶች ፣ችቦዎች እና እጣኖች ተደምረው ተዋሕደው በኅብረት ነደው እና ጨሰው በአይሁድ ቅንዐት ለ300 ዓመታት ያክል በቆሻሻ እና በአራሙቻ የተቀበረውን የክርስቶስ መስቀል ያለበትን ቦታ ያመላከቱ እና ከባዱን የፍለጋ ጉዞ ያቃለሉ የእውነት ስብስብ ናቸው፡፡

ድር ቢያብር ፣አንበሳ ያስር እንዲሉ ቀጫጭን ድሮች በኅብረት ተደመረው አንበሳን ያክል ጀግና እንደሚያስሩ ሁላችንም ከተባበርን እና አንድ ከሆንን የማናስረው እና የማንገታው ጀግና እንድሁም የማናሸንፈው ኃይል የለም በተጨማሪም ጋን በጠጠር ይደገፋል እንደሚባል የጠጠሮች ስብስብ ጋንን እንደሚደግፍ ሁሉ ፤የሁላቻንም መሰባሰብ ፣መደመር እንዲሁም መዋሐድ ሀገርን ይደግፋል፣ያቀናል፤ጠላትን ባለበት ለማስቆም እና አስሮ ለመጣል ያመች ዘንድ እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ድር መዋሐድ ፣መገመድ ፤ሀገርን ለማቆም እንደ ጠጠሮቹ መደጋገፍ እና መተባበር ይኖርብናል።
ኢትዮጵያዊነት ቋንቋችንን ሣይጠቀልለው፤ቋንቋችን ኢትዮጵያዊነትን ሳይከፍለው በኅብረት እንዋሐድ ለሀገራችን ሰላም: ለሀገራችን ሉዓላዊነት አንድ እንሁን።

በመጨረሻም በክርስቲያኖች ዘንድ ልዩ ትርጉም ያለው የመስቀሉ በዓል ዲያብሎስ የተሸነፈበት የራቀው የቀረበበት ወዳጣነው የቀደመ ርስታችን የተመለስንበት የደኅንነታችን አርማ የሆነው ቅዱስ መስቀል፤መስቀሉን ወደ ኢትዮጵያ ያመጡ ነገስታትን ባፈራች እና ብርሃን በወረደባት በደብረ ብርሃን የመስቀል በዓልን ለማክበር የተገኛችሁ ሁላችሁ እንኳን አደረሳችሁ ፡፡
መልካም የመስቀል በዓል

(የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ካሣሁን እምቢአለ)

"አራምባና ቆቦ"የሚለው አባባል ከየት እንደመጣ ታውቃላችሁ? አንኮበርን አካለው ከያዙት ሰማይ ጠቀስ ተራራዎች መሐል እመ ምሕረት የተሰኘው ከፍታው ከባህር ጠለል በላይ 3500 ሜትር የሆነው ተ...
22/09/2022

"አራምባና ቆቦ"
የሚለው አባባል ከየት እንደመጣ ታውቃላችሁ?

አንኮበርን አካለው ከያዙት ሰማይ ጠቀስ ተራራዎች መሐል እመ ምሕረት የተሰኘው ከፍታው ከባህር ጠለል በላይ 3500 ሜትር የሆነው ተራራ በሰሜን እና ደቡብ ቅርብ አቅጣጫ መሐል ለመሐል ከፍሏቸው የተጋጠሙ ኹለት አካባቢዎች ለዚህ አባባል መነሻ ናቸው- ሐርአምባ እና ቆቦ።

እኒህ ኹለት መንደሮች ብዙ የተራራቁ አይደሉም። ነገር ግን ኹለቱንም ግዙፉ የእመ ምሕረት ተራራ ጋርዶ አለያይቷቸዋል። እነዚህን ኹለት መንደሮች በአንድ ዕይታ ለመመልከት ግን ብቸኛው ቦታ ራሱ ይህ ተራራ ነው።

ቅርብ ሆነው የተራራቁትን አንድ አድርጎ የሚያሳየው ይህ የእመ ምሕረት ተራራ በርካታ የመካከለኛው ዘመን እና የጥንታዊ ኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርሶች፤ በርካታ የማያሻሙ የታሪክ ምስክሮችን የያዘ መካን ነው።

አፄ ዘርዓያዕቆብ ንግስናቸውን አክሱም ላይ ተቀብተው ከማጸደቃቸው አስቀድሞ ንጉስ የተባሉት ቀድመው ነበር። የንግስናቸውም ቦታ እዚሁ እመ ምሕረት ግድም ባለ የተጉለት ግዛት ውስጥ እንደኾነ ይነገራል። ግማደ መስቀሉም የንጉሥ ልጅ በመኾናቸው ሳቢያ በግዞት ታስረው ወደቆዩበት የግሸን አምባ ከመዛወሩ በፊት በዚሁ በእመ ምሕረት ተራራ ላይ አቆይተውት እንደነበር መጽሐፈ ነገስት ያትታል።

እመ ምሕረት የመስቀል ደመራ ቋሚ ክብረ በዓል የተደረገበት፣ በኢትዮጵያም የመጀመሪያው የመስቀል በዓል የተከበረበት ቦታ እንደኾነም ይነገራል።

አራምባና ቆቦ ቅርብ ለቅርብ ኾነው ሳለ ነገር ግን ተራርቀው እንደመኖራቸው ኹሉ የተቀራረብነውን ያራራቀን መንፈስ ተሰብሮ ሕብረታችን እንዲታይ እመ ምሕረት ላይ ኹላችንንም ለመውጣት ያብቃን።

መልካም በዓል!!!
ሰላም ለኢትዮጵያ!!!

(ያሬድ ሹመቴ)

እንሳሮ: የተስፋ ምድር(አሰግደው ሽመልስ)እንሳሮ 🌾 የሣር ምድር ይሏታል፤ የተዘባነነች ቅንጡ ናት።ላዩን ከመንዝና ጅሑር የተንደረደረው ዠማ ወንዝ ያረሰርሳታል፣ እንደገነት ዙሪያዋን ያጠጣታል፣...
20/09/2022

እንሳሮ: የተስፋ ምድር

(አሰግደው ሽመልስ)

እንሳሮ 🌾 የሣር ምድር ይሏታል፤ የተዘባነነች ቅንጡ ናት።

ላዩን ከመንዝና ጅሑር የተንደረደረው ዠማ ወንዝ ያረሰርሳታል፣ እንደገነት ዙሪያዋን ያጠጣታል፣ የዕረፍት ውኃዋም ነው።

ላዩን እነዋሪና ደነባን ተንተርሳ፣ ማዶ የመርሐቤቴን ፌጥራ እና የዞማ ተራራ ግርጌ ጌጥ ዓለም-ከተማን ታማትራለች።

በረዥሙ ሲመለከቱ፣ ከዘረት እስከ ዶባ፣ ከኮላሽ እስከ አህያ-ፈጅ ክርክም ክርክም የምድር ገፅ ይታያል።

የዠማን ወንዝ የእግሮቹን ኮቴ ተከትለው ሲወርዱ ደራ በአረንጓዴ ግምጃ ተኩሎ ግስጥ! ብሎ ይገኛል።

መሳ-ለመሳ ነው እንሳሮና ደራ፣
የሚበቅልበት የወንዶች አውራ፤

እየተባለም ይነገርለታል።

እንሳሮ የተስፋ ምድር ነው።

75,315 ሕዝብ የሚኖርበት በውኃ የተከበበ ምድር።

ጤፍ፣ ማሽላ፣ ስንዴ እና የበልበሊት ፍራፍሬ ዋነኛ ምርቶች ናቸው። ግና #ዘመናዊ ማምረቻና ይሻሉ።

ሰቃ መድኃኒትዓለም፣ ጥንታዊው በልበሊት እየሱስ ገዳም፣ ጀር ሥላሴ (የወንድ መነኮሳት ገዳም)፣ አቧራኮ ዋሻ (ሶረኔ ቆቅ በዓለማችን በብቸኝነት የምትታይበት)፣ ገዛ ዋሻን የመሳሰሉ መስህቦች አሉት።

በማዕድን ልማት በተለይ #በላይምስቶን፣ #ጂፕሰም፣ ፣ የመስተዋት እና የሞባይል ስክሪን ጥሬ እቃ፣ የፈሳሽ ሳሙና ግብዓት፣ ሲልካ አሸዋ፣ ኦፓል፣ የተፈጥሮ ጋዝ እና የቅርፅ ድንጋይ መገኛው #እንሳሮ ነው።

135 ኪ.ሜ ከአ.አ እንዲሁም ከደብረብርሃን 80 ኪ.ሜ ብቻ ይርቃል።

እልል ያለ አስፋልት መንገድ እያለቀ ነው!

ሆቴሎች አሉ የቱሪስት ማረፊያ ተጨማሪ አገልግሎት ሰጪ ተቋም እንዲመጣ ፍላጎት አለ።

በመገንባት ሂደት ላይ ያሉ 15 በላይ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ።

ለሚ ሲሚንቶ አ.ማ በ2.2 ቢሊዮን ዶላር ሥራ ጀምሯል።

እንሳሮ ሲሚንቶ በ5 ቢሊዮን ብር ሥራ ለመጀመር በሒደት ላይ ነው።

እንሳሮ: የተስፋ በሮችሽ ክፍት ናቸው።

የደብረብረሃን የቱሪዝም መዳረሻ ልማት ፕሮጀክትን ይደግፉ
20/09/2022

የደብረብረሃን የቱሪዝም መዳረሻ ልማት ፕሮጀክትን ይደግፉ

ኮረማሽ የዓፄ ምኒልክ የጦር መሣሪያ ግምጃ  ኮርማሽ የዳግማዊ ዓጼ ምኒልክ የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤት ነው፤ በአማራ ክልል ሸዋ በሀገረማርያም ከሰም ወረዳ ኮረማሽ ከተማ ይገኛል፡፡ ከአዲስ አበባ...
20/09/2022

ኮረማሽ የዓፄ ምኒልክ የጦር መሣሪያ ግምጃ ኮርማሽ የዳግማዊ ዓጼ ምኒልክ የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤት ነው፤ በአማራ ክልል ሸዋ በሀገረማርያም ከሰም ወረዳ ኮረማሽ ከተማ ይገኛል፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ብርሃን አቅጣጫ በ88 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
ጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቱ 15 ሺህ 595 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈና የዙሪያ ርዝመቱ 532 ነጥብ 3 ሜትር የሆነ ግቢ ነው፡፡

የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቱ የተመሠረተው በ189ዐ ዓ.ም መሆኑን የሚናገር ገና መግቢያ በሩ ላይ የተለጠፈ ጽሑፍ አስረዳል ።ለጦር መሳሪያ ግምጃ ቤቱ ዋነኛ መመሥረት ምክንያት የዓድዋ ጦርነት ነው፡፡
ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ የዓድዋን ጦርነት ድል ካደረጉ በኋላ ጠላት ዳግመኛ ቢመጣ የሚመክቱበት ጦር መሣሪያ ማከማቻ የሚሆን፣ ጠላት በቀላሉ የማይደርስበት ስትራቴጂካዊ ቦታ እንደሚያስፈልጋቸው ያስቡ ነበር፡፡ ለዚህም ሹማምንቱን ያማክሩ ነበር፡፡ በተለይም የቡልጋው ገዥ ራስ ዳርጌ ሳኅለሥላሴም ከግዛታቸው ምቹ የሆነ ቦታ እንዳለ አሳወቋቸው፤ ንጉሡም በተሰጣቸው ጥቆማ መሠረት ቦታውን ሄደው ዓይተው ተስማሚ መሆኑን አረጋገጡ፡፡

እስከዚያም ጊዜ ይህን ስትራቴጂክ ቦታ ባለማየታቸው ተገርመው “ሳላይሽ” ብለው ስም እንዳወጡለት ታሪክ ይናገራል፡፡ እስከ አሁንም የቦታውና የከተማው ስያሜ “ሳላይሽ” በመባል ይታወቃል፡፡

ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ቦታውን ካዩበት ጊዜ አንስተው የመገንቢያ ቁሳቁስ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገር ድረስ አሰባስበዋል፡፡

ቤቱ የተሠራው ከጭቃ፣ ድንጋይ፣ እንጨት እና ቆርቆሮ ነው፡፡ ለፎቅ ቤቱ ርብራብ እንጨት በሰው ኃይል ቀረበ፤ ቆርቆሮ እና ሚስማር ከፈረንሳይ እስከ ጅቡቲ ከዚያም እስከ ኮረማሽ (የጦር ግምጃ ቤቱ እስካለበት) ደግሞ በ500 ግመሎች ተጓጓዘ፡፡

ቤቶቹ 16 ሜትር በ8 ሜትር የወለል ስፋት እና አራት ሜትር ከፍታ አላቸው፡፡ የምድር ቤትና ፎቅ ናቸው፡፡ በውስጣቸውም በድንጋይ የተገነቡ ሁለት ሁለት እንደ ምሰሶ የሚያገለግሉ የፎቁ ርብራብ ያረፈባቸው ግርግዳዎች ይታያሉ፡፡

የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቱ በተሠራ ጊዜም የንጉሡ ታማኝና ታዛዥ አገልጋዮች ከ14ቱም ክፍላተ ሀገራት በአንድ ጋሻ መሬት ክፍያ እንደመጡ ታሪክ ያወሳል፡፡ ግምጃ ቤቱ ተሠርቶ ከተጠናቀቀ በኋላ የዲኘሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን በመቀጠል ከፈረንሳይ ሀገር የጦር መሣሪያ በማምጣት እንዳከማቹበት መረጃዎች ይገልፃሉ፡፡

ግምጃ ቤቱ ተገንብቶ በ189ዐ ዓ.ም ተጠናቀቀ፤ መሣሪያው ተጓጉዞ ሥፍራው ከደረሰ ሁለት ዓመታት ጀምሮ ለ36 ዓመታት በጦር መሣሪያ ግምጃ ቤትነት አገልግሏል፡፡ በ1928 ዓ.ም ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረች ጊዜም በግምጃ ቤቱ የነበሩ የጦር መሳሪያ ወደ በአካባቢው አምስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኝ ኮረማሽ ዋሻ እንደተወሰደና ቀሪውንም ለአርበኞች መዋጊያ እንደተከፋፈለ ይነገራል፡፡

ወራሪው ኃይልም በግምጃ ቤቱ የጦር መሣሪያ እንዳላገኘ ይነገራል፡፡ ወራሪው የጣሊያን ጦር ከሀገር ከተባረረ በኋላም እስከ 1954 ዓ.ም ድረስ በጦር ካምፕነት ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ የጦር ካምፑ ወደ አሌልቱ ሲዛወር የቡልጋ ገዥዎች መቀመጫ በመሆን አገልግሏል፤ በደርግ መንግሥትም የሕዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽና ለተለያዩ የቢሮ አገልግሎቶች ይሰጥ ነበር።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይህን ታሪካዊ ስፍራ በተለይም ጉዞ አደዋ አዘጋጆች በያመቱ የተለያዮ ፕሮግራሞችን እያዘጋጁ አካባቢውን እንዲታወቅ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል ለዚህ ተግባራቸው ምስጋና ይገባቸዋል ።

ነገር ግን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም እስካሁን ቸል ማለቱ እና ትኩረት አለመስጠቱን አምኖ ቀጣይ ለጎብኝዎቹ ምቹ መንገድ ውኃ ኔትዎርክ የመሳሰሉትን እንዲሟሉ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራበት ይገባል ።

ሸዋ ጠቅላይ ግዛት _ቡልጋ


𝓫
Visit Shoa Amara
𝓽

𝓽

𝔂

19/09/2022

ሸዋ የንጉሳውያን የእራት ምሽት

መስከረም 17 ቀን 2015 ዓ.ም በአርትስ ቴሌቪዥን ይጠብቁ

19/09/2022

ሸዋ የንጉሳውያን የእራት ምሽት

መስከረም 17 ቀን 2015 ዓ/ም በአርትስ ቴሌቪዥን ይጠብቁ!

ስለ ግሼን የግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ አመጣጥ፤======================ግሼን ደብረ ከርቤ እንዴት እና መቼ እንደደረሰ፤======================የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመ...
19/09/2022

ስለ ግሼን

የግማደ መስቀሉ ወደ ኢትዮጵያ አመጣጥ፤
======================
ግሼን ደብረ ከርቤ እንዴት እና መቼ እንደደረሰ፤
======================
የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን የማይሽረው ሚና፤
======================

(በውብሸት ሙላት)

የዚህ ጽሑፍ ምንጭ ‘’መጽሐፈ ጤፉት’’ ስለሆነች በቅድሚያ ስለመጽሐፏ ጥቂት ነጥቦችን ማንሳቱ ተገቢ ነው፡፡ ግሼን ደብረ ከርቤ ማርያም፣ለመስከረም 21 ንግሥ የሄደ ሰው ስለዚች መጽሐፍ ላይሰማ አይችልም፡፡ በዕለቱ በአደባባይ ስትነበብ፣ስትተረክ፣ስትተረጎም ትውላለች፤በደብሩ ሊቃውንት፡፡ እኛም ስለዚች መጽሐፍ ከልጅነታችን ጀምረን ስትጠራ የሰማነውና የማናውቀው በአንስታይ ጾታ ስለሆነ የተለመደው አጠራር መጠቀም ተመርጧል፡፡

የመጽሐፈ ጤፉት ስያሜ የመነጨው ከጽሑፉ ደቃቅነት ነው፡፡ ፊደላቱ እንደጤፍ ቅንጣት ቢያንሱ፣ድቅቅ ቢሉ “መጽሐፈ ጤፉት” ተባለች፡፡ የመጽሐፏ ይዘት ወይም መጠን ግን ትንሽ አይደለም፡፡ሙሉው የብራና መጽሐፍ ዳጎስ ያለ ነው፡፡

መጽሐፈ ጤፉት በአንድ ጊዜ፣አልተጻፈችም፡፡ ይሁን እንጂ ብዙው ክፍሏ በአንዴ የተጻፈ ይመስላል፡፡ የመጽሐፈ ጤፉት ደራሲም ታላቁ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ መሆኑን ለማወቅ ብዙ አዳጋች አይደለም፡፡ የተጻፈበትን ሁኔታም፣የደራሲውንም ማንነት በተመለከተ መጽሐፉን ያነበበ ማንም ሰው ይሄንን በቀላሉ ይረዳዋል፡፡

ለዚህ ጽሑፍ በምንጭነት ያገለገለው በመሪጌታ የማነ ብርሃን ተተርጉሞ፣በግሼን ደብረ ከርቤ ደብር ሰባካ ጉባኤ አማካይነት በ2006 ዓ.ም. የታተመው ነው፡፡ መጽሐፏ የተወሰኑ ቦታዎች የምትሸጥ ቢሆንም በሶፍት ኮፒም ትገኛለች፡፡

በመጽሐፈ ጤፉት ላይ፣ መስቀሉ ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለበት በኋላ ጠፍቶ እንዴት፣የት እና መቼ እንደተገኘ ተገኘ ተገልጿል፡፡ ወደ ግብጽ መቼና እንዴት እንደተወሰደም ተተርኳል፡፡ ከግብጽ እንዴት ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ፣ ግሼን ደብረ ከርቤ እንዴት እንደደረሰ እና የነገሥታቱ በተለይምም የዓፄ ሰይፈ አርዓድ፣የዓፄ ዳዊት ካልእ እና የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ሚና ምን እንደነበር ተወስቷል፡፡

ግሼን ከደረሰ በኋላ እንዴት እንተቀመጠ፣የት እንደተቀመጠ፣ለመስቀሉ ደኅንነትና ጉዳት እንዳይደርስበት ምን መደረግ እንደሚገባ ትዕዛዛት ተላልፈዋል፡፡ የደብሩና የአምባሰል አስተዳዳሪ (የዣንጥራሩ) ግንኙነት ምን መሆን እንዳለበትም ንጉሣዊ ድንጋጌዎች አሉት፡፡ በወቅቱ፣ከአምስት መቶ በላይ የሚሆኑ የነገሥታቱ ቤተሰቦች በአምባው ላይ ይኖሩ ስለነበር እነሱንም የሚመለከት ሕግጋት ተሠርቷል፡፡

ታሪኩንም ደንቡንም የጻፈው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ነው፡፡ ንጉሠ ነገሥቱ፣ መስቀሉ ከግብጽ እንዴት እንደመጣ፣ግሼን እንዴት እንደደረሰ፣ቤተ ክርስቲያናቱ ስለታነጹበት ሁኔታ፣መስቀሉ እንዴት እንደተቀመጠ የሚያትቱን ክፍሎች እዚያው በደብሩ እያሉ የተጻፉ ይመስላል፡፡ የመስቀሉን የቀደመ ታሪክ እንዲሁም የደብሩን እና የዣንጥራሩን ግንኙነት ደግሞ ኋላ ከደብረ ብርሃን (ከዋና ከተማው) ሆኖ በሌላ ጊዜ የላካቸው ይመስላል፡፡ እስኪ ስለመስቀሉ የሦስቱን ነገሥታት ሚና በቅድሚያ እንመለከት፡፡

ዓፄ ሰይፈ አርዓድ (1328-1356)፤
=================

ንጉሡ፣ ወደ ምስር (ግብጽ) ወርደው እንደነበር መጽሐፈ ጤፉት ላይ ተገልጿል፡፡ የሔዱትም በዘመቻ መልክ ነው፡፡ የወቅቱ የግብጽ ንጉሥ (መርዋን አልጋዲን) ከኢትዮጵያ ጋር በሃይማኖት አንድ በሆኑት በእስክንድርያ ሕዝበ ክርስቲያን ላይ አገዛዙን ከማጽናቱ ባለፈ የእስክንድርያውን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሚካኤልን (47ኛው ሊቀ ጳጳስ) ስላሰራቸው ለማስፈታት ወደ ግብጽ ዘምቷል፡፡

የግእዙ ንባብ እንዲህ ይላል፡፡

“ወሶበ ሰምዓ ንጉሠ ኢትዮጵያ ሰይፈ አርዓድ ከመ ኰንንዎ መኳንንተ ተንባላት ለዝንቱ አብ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል ወሞቅሕዎ፡፡ ቀንዓ ቅንዓተ መንፈሳዊተ በእንተ ዘዘኮነ እስክንድርያ ወኢትዮጵያ አሐተ ሃይማኖተ፡፡ ወወረደ ብሔረ ግብፅ ዘምስለ ብዙኃ ሠራዊት፡፡”

ታሪከ ነገሥቱም ቢሆን ንጉሡ ወደ ግብፅ መውረዳቸውን ይገልጻል፡፡ ልዩነታቸው የታሰሩት ሊቀ ጳጳስ ስም ላይ ብቻ ነው፡፡ በታሪከ ነገሥቱ የሊቀ ጳጳሱ ስም አባ ማርቆስ ነው፡፡

ዓፄ ሰይፈ አርዓድም ግብፅ ወርደው ለመርዋን አልጋዲን ጳጳሱን ከእስር እንዲፈታ ካልሆነ ግን በመካከላቸው ፍቅር እንደማይኖር ስለጻፈላቸው ከእስር ፈቷቸው፡፡ ንጉሡም ለሊቀ ጳጳሱ እጅ መንሻ ወርቅ ልከው ወደ አገራቸው ተመለሱ፡፡ ስለሆነም፣በመጽሐፈ ጤፉት መሠረት በዐፄ ሰይፈ አርዓድ ዘመን መስቀሉ አልመጣም፡፡ ይሁን እንጂ፣ታሪኩ ከላይ በቀረበው መልኩ ተካትቷል፡፡

ዓፄ ሰይፈ አርዓድም በ1328 ዓ.ም. ነግሠው 28 ዓመታት ከገዙ በኋላ እንዳረፉ መጽሐፏ ገልጻለች፡፡ ቀጥሎም ልጃቸው ውድም አስፈሬ ለ10 ዓመታት ነግሷል፡፡

ዳግማዊ ዓፄ ዳዊት (1366-1397)፤
=================

መጽሐፈ ጤፉት፣ እንደመጽሐፍ የተጻፈችበት ምክንያትን እንዲህ በማለት ይጀምራል፡፡

“… ንዌጥን በረድኤተ እግዚአብሔር ሕያው ዘከመ ተረከበ መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ መንግሥቱ ለዳግማዊ ዳዊት….ወዘከመ መጽአ ውስተ ብሔረ ኢትዮጵያ በመዋዕለ መንግሥተ ወልዱ ዘርዓ ያዕቆብ፡፡ ወቦአ ውስተ ደብረ ነገሥት አሀገረ አምባሰል፡፡”

የአማርኛ ትርጉሙም እንዲህ ነው፡፡ “በዳግማዊ ዳዊት ዘመነ መንግሥት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል እንደተረከቡ፤ልጃቸው ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ በነገሡበት ዘመንም ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ አምባሰል ደብረ ነገሥት እንደገባ (እንደተቀመጠ) እንናገራለን፡፡”

ከዚህ የምንረዳው ዓፄ ዳዊት መስቀሉን ከግብፆች ተረክቧል፡፡ ይኹን እንጂ፣በዓጼ ዳዊት ዘመን ወደ ኢትዮጵያ አልገባም፡፡

ታዲያ ዓፄ ዳዊት ተረክበውት ከነበረ፣ ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ እስኪነግሥ (ቢያንስ ለ35 ዓመታት ያህል የት እንደነበር አሁንም በመጽሐፈ ጤፉት በዝርዝር ተተርኳል፡፡ ታሪኩም በአጭሩ እንዲህ ነው፡፡

የምስሩ ንጉሥ፣ ዓፄ ሰይፈ አርዓድ መሞቱን ሲሰማ በድጋሜ ጳጳሱን አሰሯቸው፡፡ በዚህን ጊዜም ከምስር ሕዝበ ክርስቲያን በተጨማሪ የሮም፣የቁስጥንጥንያ፣የሶሪያና አርመን ክርስቲያኖች በግብፁ ንጉሥ ድርጊት ምክንያት መስቀሉን መሳለም እንዳልቻሉ እና የኢትዮጵያን ንጉሥ እንዲረዷቸው ጥያቄ አቀረቡ፡፡

ይኼን የሰማው፣ ለሃይማኖቱ ቀናተኛ የሆነው ዳግማዊ ዳዊት ወደ ግብፅ ዘመተ፡፡ ንጉሡም ካርቱም በደረሰ ጊዜ የዓባይን ወንዝ ወደበርሃ እንዲፈስ በማድረግ አቅጣጫውን እንዲቀየር አደረገው፡፡ ግዕዙ እንዲህ ይነበባል፡፡ “ወሶበ በጽሐ ኀበ ካርቱም ወጠነ ከመ ይሚጦ ለፈለገ ዓባይ ከመ ይክልኦሙ ማየ ፈለገ ዓባይ…”

የዓፄ ዳዊትን አድራጎት የሰማው የግብፁ ንጉሥ፣ የመርዋን አልጋዲን ልጅ አህመድ፣ ጳጳሱንም ሆነ ሌሎች እስረኞች ከእስር ለቀቃቸው፡፡ በመቀጠልም ጳጳሱንና የየአገራቱን ሕዝበ ክርስቲያን፣ ዓፄ ዳዊትን ዓባይ እንደቀድሞው እንዲፈስ እንዲሁም ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ለእጅ መንሻ የሚሆን ወርቅ በመላክ ጭምር አስለመኑ፡፡


ዓፄ ዳዊት ግን ጉዞውን ሳያቆም ወደ አስዋን ወረዱ፡፡ ወርቁንም ሳይቀበል መልሶ ላከ፡፡ የውሃውንም ፍሰት አላስተካክልም አለ፡፡ ይልቁንም “መስቀሉን ስጠኝ” በማለት መልዕክት ሰደደ፡፡ “ወንጉሠ ምስርሰ አህመድ ወመኳንንተ ተንባላት ተሐውኩ ብዙኃ በምክንያተ ዝንቱ፡፡” ይላል ግዕዙ፡፡ “በዚህም ምክንያት የአሕዛቡ የምስር ንጉሥ አህመድና መኳንንቱ ፈጽመው ታወኩ፡፡” የንጉሡን ቁርጠኝነት ሲያውቁ መስቀሉን፣ሉቃስ የሣላቸውን ሰባት የእመቤታችንን (የማርያምን) ሥዕሎች ዮሐንስ ወንጌላዊ የሣለውን ሥዕል ጨምሮ ላከ፡፡

ይህም የተደረገው መስከረም 10 ቀን ነው፡፡ ንጉሡም በዚህ ቀን ታላቅ በዓልን አደረገ፡፡ በዚህ ብቻ ሳይበቃም፣ ከመስከረም 17 ጀምሮ ለ7 ቀናት ታላቅ በዓልም ተደረገ፡፡ ከዚህ በኋላም፣ እነዚህን ቅርሶች በመያዝ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ላይ ሳለ፣ስናር የተባለ ቦታ ላይ ዓፄ ዳዊት በድንገት አረፈ፡፡ ያረፈው፣ ጥቅምት 9 ቀን ነው፡፡ ሰላሳ ዓመት፣ከ6 ወራት፣ከ9 ቀናት ገዝቶ ሞተ፡፡

በመሆኑም፣ዓፄ ዳዊት መስቀሉን የተረከበው በ1397 ዓ.ም. መስከረም 10 ቀን ሲሆን የሞተው ደግሞ በዚሁ ዓመት (ሱዳን ውስጥ) ስናር ላይ ነው፡፡ ከዚያም፣ጣና፣ ዳጋ እስጢፋኖስ ተቀበረ፡፡ (ዓፄ ዳዊት ያረፉበትን ዓመት በተመለከተ በርካታ መጽሐፍት ላይ ልዩነት እንዳለ ያጤኗል፡፡ በዚህ ጽሑፍ ላይ ግን እንዳለ የመጽሐፈ ጤፉት ነው የተገለጸው፡፡)

ታሪከ ነገሥቱ በበኩሉ ባዝራ (በቅሎ) ግምባራቸው ላይ ረግጣ እንደገደለቻቸው ይገልጻል፡፡ መጽሐፈ ጤፉት፣ በምን ምክንያት እንደሞቱ ባይናገርም፣ሊሞቱ ሲሉ በዚሁ ስናር በተባለው ቦታ ጥቅምት 9 ቀን ለልጆቻቸው የመንግሥትን ሥርዓትና ወግ ጽፈው እንዳረፉ ይናገራል፡፡ ከመሞታቸው በፊት እንደሚሞቱ ያወቁት ምናልባት የባዝራዋ ጎድቷቸው ነገር ግን በቅጽበት ባለመሞታቸው ሊሆን ይችላል፡፡

ይሁን እንጂ ንጉሡ ሲሞቱ ቅርሶች አብረው አልመጡም፡፡ ዘርዓ ያዕቆብ እስኪነግሥ ድረስ እዚያው ስናር እንደቀሩ አሁንም መጽሐፈ ጤፉት ትነግረናለች፡፡ በዳዊትና በዘርዓ ያዕቆብ መካከልም ሌሎች ልጆቹ እንደነገሡም እንዲሁ ተተርኳል፡፡

በመሆኑም፣መስቀሉንም ሆነ ሌሎቹ ቅርሶችን ዓፄ ዳዊት ተረክቧቸው ነበር፡፡ ነገር ግን በንጉሡ ድንገተኛ ዕረፍት ምክንያት ስናር ላይ ቀሩ፡፡

ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ (ከ1427 ጀምሮ)፤
==================

ዓፄ ዳዊት በስናር አርፎ በዳጋ እስጢፋኖስ ሲቀበር መስቀሉ እና ሌሎቹ ቅርሶች እዚያው ስናር እንደቀሩ ተገለጿል፡፡ ዓፄ ዳዊት በሕይወት በነበረበት ወቅት “ይነብር መስቀልየ በዲበ መስቀል” የሚል ህልም ዐይቶ እንደነበር ተጽፏል፡፡ ትርጓሜውም “መስቀሌ በመስቀል ላይ ይቀመጣል፤” ነው፡፡

ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብም በ1427 ዓ.ም. ነገሠ፡፡ ኋላ ላይ እንደ አባታቱ ህልም ተገለጠለት፡፡ ይህ የኾነው ደግሞ በነገሠ በ15 ዓመቱ ነው፡፡ 1442 ዓ.ም. መሆኑ ነው፡፡ ህልሙም፣ “አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል” የሚል ነው፡፡ ትርጓሜውም “መስቀሌን በመስቀል ላይ አኑር/አስቀምጥ!” የሚል ነው፡፡ ለአባታቱ በትንቢትነት፣ወደ ፊት በሚፈጸም መልኩ የታየው ህልም፤ ለዘርዓ ያዕቆብ በትእዛዝነት ተገለጠ፡፡

ንጉሡም ከሊቃውንቱ ጋር በመመካከር፣ስለ ህልሙ ሲያወጣና ሲያወርድ አንድ ዓመት አለፈ፡፡ ከዚያም፣ሊቃውንቱና የመንግሥቱ አማካሪዎች ፍቹን ነገሩት፡፡ “ወእሙንቱኒ ይቤሉኒ እስመ መስቀለ ክርስቶስ አምኃሁ ለአቡከ ሀሎ በእደ መኰንነ ተንባላት ዘመካ መዲና” ብለው ለገሩኝ ሲሉ ራሳቸው ንጉሡ ተናግረዋል፡፡ ትርጓሜውም፣ “እነሱም ይኽማ ለአባትህ እጅ መንሻ ሆኖ የመጣው የክርስቶስ መስቀል በመካ መዲናው ሹም እጅ አለና አምጣ!” ሲልህ ነው ይሉታል፡፡

ከዚያም ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብም “ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት” በማለት ወደ መካ መዲናው ሹም ዘመቻ ጀመሩ፡፡ የመካና መዲናው ሹም ስምም ‘ጋፍሔር’ ይባላል፡፡ በዚያን ዘመን የነበረው የምስሩ ንጉሥ ደግሞ ‘አሽረፍ’ ነበር፡፡ ከጽሑፉ መረዳት የሚቻለው ጋፍሔር፣በንጉሥ አሽረፍ ሥር የነበረ ገዥ መሆኑን ነው፡፡

ጋፍሔርም፣የዘርዓ ያዕቆብን መምጣት ሲሰማ “የአባትህ ገንዝብ በእጄ አለና ተቀብለህ ወደ አገርህ በሰላም ተመለስ” የሚል መልዕክት ላከለት፡፡ ዘርዓ ያዕቆብም መስቀሉን፣ ሰፍነጉን፣ ከለሜዳውን፣ ሥዕሎቹን፣ የቅዱሳኑን አጽም እና ሌሎችንም በመቀበል ከነሠራዊቱ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ፡፡

ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ በኋላ ለሦስት ዓመታት ያህል በየተራራው በመዞርና በማሳረፍ እንደ ህልሙ ለመፈጸም ንጉሡ ጥሯል፡፡ ከሦስት ዓመታት መንከራተትና ልፋት በኋላ እስከ ዓፄ ይኩኖ አምላክ ድረስ ደብረ ነጎድጓድ፣ቀጥሎም ደብረ ነገሥት የተባለችው የአሁኗ ግሼን ደብረ ከርቤ አምባ ላይ ደረሰ፡፡ የተራራውን ግርጌ በመከተል ሦስት ጊዜም ዞራት፡፡ድጋሜ ከመልአክ በህልም ትእዛዝ ከተቀበለ በኋላ ከወቅቱ ጳጳሳት ከአባ ሚካኤል እና ከአባ ገብርኤል ጋር በመሆን ወደ አምባው በ1446 ዓ.ም. መስከረም 21 ቀን ገቡ፡፡

ከአምባው ላይ ቀደሞ በ514 ዓ.ም. በዓፄ ካሌብ ዘመን፣በአባ ፈቃደ ሥላሴ፣የናግራን መነኩሴ አማካይነት የተተከሉ የማርያምንና የእግዚእብሔር አብ ቤተ ክርስቲያናት ስለነበሩባቸው የእግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያንን ድጋሜ በማሳነጽ በመሠረቱ ሥር መስቀሉንና ሌሎቹን ቅርሶች አስቀመጣቸው፡፡

የቤተ ክርስቲያኑ ግንባታም ሦስት ዓመታት ፈጅቷል፡፡ ቤተክርስቲያኑ የነበረበት ቦታ ርጥበት ያለበት ስለነበር ርጥበቱን የሚያጠፋ አፈር አድርገውበታል፡፡ ለመስቀሉ እና ለሌሎች ቅርሶች ማስቀመጫ ይሆን ዘንድ አርባ ክንድ ወርድ፣ርዝመትና ከፍታ ያለው ጉድጓድ በማስቆፈር እና ዙሪያውን በመገንባት ርጥበቱም እንዲጠፋ በሰማንያ ስምንት ግመሎችና በመቶ አጋሰስ ከኢየሩሳሌም አፈር በማስመጣት ለግንባታው ውሏል፡፡

ከዚያም መስቀሉን፣ሥዕላቱን፣የቅዱሳኖቹን አጽም፣ሰፍነጉን፣ጅራፉን፣ከለሜዳውን ወዘተ በምን ሁኔታ እንደተቀመጠ በዝርዝር ተገልጿል፡፡ የእነዚህ ቅርሶች ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ ለጉዳትም ለመቅሰፍትም ስለሚሆን ጊዜው እስኪደርስ ማንም እንዳያወጣቸው ትእዛዝ ተበጅቷል፡፡ በተለይ መስቀሉ በተለያዩ ሁኔታ ከተዘጋጁ ድርብርብ ሳጥን ውስጥ ሌላ የወርቅ እና የዕንቁ ሳጥን በማዘጋጀት በውስጡም በሰንሰለት በማሰር በአየር ላይ ብቻ እንዲረብ (እንዲጠለጠል) መደረጉን ተጽፏል፡፡

መስቀሉም ሲመጣ፣ እንደሰው እንዲቆም አድርገው የውጮቹ ጠቢባን ሰገባ እና እግር እንዳዘጋጁለትም ተገልጿል፡፡ በመጨረሻም፣የጉድጓዱ አፍ ተዘግቶ በላዩ ላይ ድጋሜ የእግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን ታነጸ፡፡ የማርያምን ቤተክርስቲያንም እህቱ ዕሌኒ (ሚስቱ አይደለችም) በድጋሜ አሳንጻው አብረው በ1449 ዓ.ም. መስከረም 21 ቀን ተመረቁ፡፡ ቅዳሴ ቤታቸው በድጋሜ ተከበረ፡፡

ሲጠቃለል፣መስቀሉንና ሌሎች ቅርሶችን ዓፄ ዳዊት በ1397 ዓ.ም. መስከረም 10 ቀን ተረክቧል፡፡ ነገር ግን፣ስናር ላይ ሲደርስ ስላረፈ እነዚህ ቅርሶችም እዚያው ለ46 ዓመታት ይህል በአሕዛብ እጅ ሰንብተዋል፡፡ ኋላ ላይ በ1443 ዓ.ም. ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ከነበሩበት ቦታ በመስመጣት በ1446 መስከረም 21 ቀን አምባሰል፣ደብረ ነገሥት (ደብረ ከርቤ ብለው የሰየሟት) ደርሷል፡፡ ንጉሡም አብሮ በመሔድ፣ቤተክርሰቲያኑንም አሳንጿል፡፡ ሥርዓቱንም አብጅቷል፡፡

መስቀሉ መስከረም 21 ቀን ግሼን ደብረ ከርቤ ደረሰ፡፡

ቤተ ክርስቲያናቱ ከእንደገና ታንጸው፣መስቀሉም በክብር ተቀምጦ ክበረ በዓሉ የተከናወነው መስከረም 21 ቀን ነው፡፡

መስከረም 21 ቀን ምን ጊዜም ግሼን ትከበራለች፡፡

ዓፄ ዘርዓ ያዕቆብን ክፍሉን ከጻድቃኑ ጋር ያድርግለን።

ደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም
15/09/2022

ደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም

ልዩ ነን፣ ወርቅ ነን!ሐበሻ ቢራ
14/09/2022

ልዩ ነን፣ ወርቅ ነን!

ሐበሻ ቢራ

13/09/2022

የደብረብረሃንን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም ይደግፉ።

መልካም አዲስ አመት!

ፕሮጀክታተችን በእራት ዝግጅቱ ለነበሩ ተሳታፊዎች አጋዦች ለእልፍኝ አስከልካዮች ለአጋፋሪዎች ለንጉሥ ጠባቂዎች ለአሳላፊዎች ሁሉ የከበረ ምስጋና አለው።ሸዋ አፍላገ- ነገሥታት!
12/09/2022

ፕሮጀክታተችን በእራት ዝግጅቱ ለነበሩ ተሳታፊዎች አጋዦች ለእልፍኝ አስከልካዮች ለአጋፋሪዎች ለንጉሥ ጠባቂዎች ለአሳላፊዎች ሁሉ የከበረ ምስጋና አለው።

ሸዋ አፍላገ- ነገሥታት!

ለመላው ቤተሰቦቻችንና አጋሮቻችን መልካም አዲስ አመት እንመኛለን።አመቱ የፍቅር የአንድነት የሠላምና የከፍታ ይሁን!የደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም!
10/09/2022

ለመላው ቤተሰቦቻችንና አጋሮቻችን መልካም አዲስ አመት እንመኛለን።

አመቱ የፍቅር የአንድነት የሠላምና የከፍታ ይሁን!

የደብረብረሃን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም!

የሸዋ ቱሪዝምና ኢንቨስትመንት አምባሳደር
10/09/2022

የሸዋ ቱሪዝምና ኢንቨስትመንት አምባሳደር

የደብረብረሃንን  ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም ይደግፉ!ታሪካዊውን ቅርስ የመጠበቅ የቱሪዝም መዳረሻ የማስፋፋትና የማረበረታታት ንቅናቄን ይቀላቀሉ!
09/09/2022

የደብረብረሃንን ቱሪዝም ልማት ፕሮግራም ይደግፉ!

ታሪካዊውን ቅርስ የመጠበቅ የቱሪዝም መዳረሻ የማስፋፋትና የማረበረታታት ንቅናቄን ይቀላቀሉ!

09/09/2022
የቱሪዝም ልማት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በስኬት ተጠናቀቀበደብረብርሃን ከተማ ከሚገኙ በርካታ ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊ፣ ኃይማኖታዊና ትውፊታዊ ቅርሶች ውስጥ የንጉስ ሣሕለሥላሴ እና ...
09/09/2022

የቱሪዝም ልማት ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሐ-ግብር በስኬት ተጠናቀቀ

በደብረብርሃን ከተማ ከሚገኙ በርካታ ታሪካዊ፣ ተፈጥሯዊ፣ ባህላዊ፣ ኃይማኖታዊና ትውፊታዊ ቅርሶች ውስጥ የንጉስ ሣሕለሥላሴ እና የዳግማዊ ምኒልክ የመጀመሪያው ቤተ መንግስታት ፍርስራሾች በታሪካዊ ቅርስነት ተመዝግበው ተይዘዋል። እነዚህን በታሪክ ፊት ንዑዳን የሆኑ ሥፍራዎች በመጠገን፣ በማስተዋውቀና ተጨማሪ የቱሪስት መዳርሻ ማዕከል በማድረግ ቅርሶቹን መጠበቅና ለዓለም ማሳየት አስፈላጊም ነው። ቅርሶቹን በመንከባከብ እና በመዳረሻነት በማልማት ከቱሪዝም ገቢ ማህበረሰቡም ተጠቃሚ እንዲሆን እና የሸዋን እና አካባቢወን መዳረሻ ስፍራዎችን በማስተሳሰር የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም እጅጉን አጋዥ ይሆናል።

ነገር ግን ይህን ለመከወን በመንግስት የሚደረገው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ማኅበረሰቡን፣ የዳያስፖራ ወገናችንን፣ ዓለም-አቀፍ ተቋማትን እና የግል ባልሀብቱን ማሳተፍ ስለሚያስፈልግ በተደራጅ መልኩ የፕሮሞሽን እና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብራት መሪ ዕቅድ ተዘጋጅቶ በ2015 የበጀት ዓመት ወደተግባር ተገብቷል። ይህ ዓለም-አቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር ዕቅድ ከረጅም ጊዜ ወይይትና መጠነ-ሠፊ መሰናዶ በኋላ ትላንት ጳጉሜ 3 ቀን 2014 ዓ.ም በደብረብርሃና ከተማ ጌትቫ ሆቴል “የሸዋ የንጉሣውያን እራት ምሽት፡ የቱሪዝም ልማት የግቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር” በሚል በይፋ ተጀምሯል።

በተለይም በደብረብርሃን ሪጅዮፖሊታን የሚገኙ ቅርሶችን፣ መስህቦችን እና የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎችን ለመጠገን፣ ለማስፋፋት፣ በተገቢው መልኩ ለማልማትና ለኅብረተሰቡ ገጽታና ኤኮኖሚ ልማት አጋዥ እንዲሆኑ ማድረግ የሚያስችል እንደሆነ የከተማው ተ/ም/ከንቲባ አቶ ካሳሁን ገልጸዋል። የዚህ የቱሪዝም ንቅናቄ የመጀመሪያ ምዕራፍ ዓላማዎች የልቼ ዳግማዊ ዐጤ ምኒልክ እና የንጉስ ሣሕለሥላሴ ቤተ መንግስታት ፍርስራሽ ቅርሶች ያሉበትን ቦታና አሁናዊ ሁኔታና ችግሩን ማሳየት፣ በስፋት በልዩ ልዩ ዘዴዎች ማስተዋወቅና ለጥገናና መልሶ ማልማት ስራ የሚያግዝ ቅስቀሳ ማድረግ፣ እና መልሶ ለማልማትና የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆኑ የሚያግዝ ፋይናንስ ማሰባሰብና ማስተዋውቅ ናቸው።

በይፋዊ የማስጀመሪያ መርሐ-ግብሩ ላይ የደብረብርሃን ከተማ እና የሰሜን ሸዋ አመራሮች፣ የአካባቢው አልሚ ባለሐብቶች፣ የሲቪክ ማኅበራት፣ የሴቶች የባሕል ቡድኖች፣ አንጋፋና ወጣት የኪነ-ጥበብ ሰዎች፣ ተጋባዥ እንግዶች፣ ምሁራንና የሚዲያ አካላት በድምሩ ከ300 በላይ ታሪክ፣ ቅርስና ቱሪዝም ልማት ደጋፊዎች ተሳትፈውበታል። በዕለቱም በታቀደው ልክ ሁሉም ተሳታፊ፣ በይፋዊ መልዕክት ከአገርውስጥና ከውጪ ሃገር እንዲሁም አልሚ ባለሃብቶች የቃልኪዳን ሰነድ በመፈረምና በቀጥታ ሰፊ ድጋፋቸውን አሳይተዋል።

ከዚህ ታላቅ የልማት ሥራ ጋር በተያያዘ የከተማ አስተዳደሩ ከያዛቸው የቱሪዝምና ኢንቨስትመንት ተመጋጋቢ ፍኖተ-ካርታ ስኬት ዓለም-አቀፋዊ የቅስቀሳ ሥራ ለመሥራት ያመች ዘንድ አርቲስት ብሌን ማሞን የቱሪዝም እና አኢንቨስትመንት ፕሮሞሽን አምባሳደር አድርጎ ሰይሟል።

ከትብብር ልማት አኳያ የከተማ አስተዳደሩ ከሰሜን አሜሪካ ኦሃዮ ግዛት የቀረበለትን የእህት ከተማ ጥያቄ ለታዳሚው አቅርበው ለቴክኖሎጂ፣ ትምህርትና ኢንዱስትሪ ልማት በጋራ እንደሚሰሩ በዕለቱ ጥያቄውን ከሰሜን አሜሪካ ይዘው ለተገኙት ልዑክ እና ታዳሚ አብስረዋል።

በክብር እንግድነት የተገኙት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር የመዳረሻ ልማት ሚንስትር ዲዔታ ክቡር አቶ ስለሺ ግርማ፣ የአብክመ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ጣሂር መሀመድ እና የሰሜን ሸዋ አስተዳዳሪ አቶ መካሻ ዓለማየሁ ለተጀመረው የቱሪዝም ልማት ፕሮግራም መሥሪያ ቤቶቻቸው የገንዘብና የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል። በዚሁ ታሪካዊ መድረክም አቶ ወርቁ አይተነው ድጋፍ እንደሚያደርጉ በተወካያቸው በኩል አሳውቀዋል።

በመጨረሻም የፕሮግራሙ ባለቤት የከተማው ባሕልና ቱሪዝም መምሪያ እንዲሁም ተጉለት ሚዲያና ፕሮሞሽንና ናብሊስ ኮሚዩኒኬሽንስ የፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ አማካሪ ድርጅቶች በማስጀመሪያው መርሐ-ግብር የታየው አበረታች ድጋፍና ተሳትፎ ወደ መላው ሕብረተሰብ እንዲሰፋ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት እንደሚሰሩ አስታውቀዋል።

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Telephone

+251991919164

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Debrebirhan Tourism Development Program posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Amhara Investment Promotion & Marketing Initiative

Welcome to the official Page of Amhara Investment Promotion & Marketing Initiative. The page is dedicated to create maximum visibility to the Amhara investment potentials and opportunities for the international business community.